lørdag 27. juli 2013

ለጸረ ሙስና እና ቤቲን እንከሳለን በማለት ለዛቱ አቃቢያነ ህጎች የቀረበች ቆንጆ ፈተና => ሰምሃል መለስ ዜናዊ

ዳዊት ሰለሞን በፌስቡክ ገጹ ያሰፈረው አስተያየት፦ 
የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ የሚያበላሽና ለህዝቡ ማህበራዊ ሞራል ተቃራኒ የሆነ ድርጊት በመፈጸሟ በወንጀል እንከሳታለን በማለት በቢግ ብራዘርስ አፍሪካ ወሲብ ስትፈጽም የታየችውን ቤቴልሄም አበራን ለመሞገት መዘጋጀታቸውን አቃቢያነ ህጎች መናገራቸውን አቤ ቶክቻው አስር አለቃ በማለት የሚጠራው አንድ የቅዳሜ ጋዜጣ ማስነበቡ አይዘነጋም፡፡
እኔ ለማህበራዊ ዕሴቶቻችን ጥብቅና ለመቆም እንዲህ ትንታግ አቃቢያነ ህጎች አለን ማለታቸውን ውድድ አድርጌዋለሁ፡፡መቼም ባለሞያዎቹ ለወሲብ ጊዜ ብቻ የህግ አንቀጽ መምዘዝ ያለባቸውም አይመስለኝም፣እናም ሰዎቹን በየትናችሁ ለማለት የሰምሃል መለስ ዜናዊ ሰሞነኛ ጉድ አሪፍ መፈተኛ ትመስለኛለች፡፡አቃቢያነ ህጎቹ የአባትን ስልጣን ተገን በማድረግ ይህችን ደሃ አገር እንደ ሸንኮራ መምጠጥ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ተቀባይነት ያገኘ የኢትዮጵያዊያን ትውፊት ነው ካላሉን በስተቀር መለስም ይሁኑ አዜብ በ2011 ኒውዮርክ ውስጥ በሚገኝ ባንክ 5 ቢልዮን ዶላር በልጃቸው ሰምሃል ስም ማስቀመጣቸውን ዶክተር መኮንን ወንድሙ ለእንግሊዝ ፓርላማ በመግለጽ የምለውን የምትጠራጠሩ ከሆነ ዶላሩ በስሟ ገቢ የተደረገበትን የቼክ ኮፒ ተመልከቱልኝ ብለዋል፡፡
በቅርቡ ሙሰኞችን ወህኒ እያወረድኩ ነው ያለን ጸረ ሙስናስ ቢሆን እንዲህ አይነት ጥብስ መረጃና ማስረጃ እየቀረበለት ምን ይጠብቃል? ዜናው ለአደባባይ የበቃበት ወቅት ግጥምጥሞሽም ሌላው አስቂኝ ነው፡፡ሰምሃል በኒውዮርክ ያጨቀችውን ዶላር ቤሳቤስቲን ሳትነካ ለአባቷ ሙት አመት የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ኪስ ለመዳበስ መንቀሳቀስ ጀምራለች፡፡እንዴት ነው ነገሩ ?ሼም የለም?

Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=5677

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar