onsdag 25. februar 2015

ኢሳት ምሽት ፕሮግራም በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ ተካሄደ


Posted: 30 Apr 2014 01:11 PM PDT

በኖርዌይ የሚኖሩትን ኢትዮጵያን ስደተኞችን የአኖኖር ሁኔታ በሚመለከት ህዝባዊ ውይይት እና የኢሳት ምሽት ፕሮግራም በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ ተካሄደ 

March 1/2014

በኖርዌይ ከተማ ኦስሎ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች በኖርዌይ የሚኖሩትን ኢትዮጵያን  ስደተኞችን የአኖኖር ሁኔታ በሚመለከት   ሐሙስ የካቲት20,2006 ዓ ም  በአንድ ላይ በመሰብሰብ ውይይት እና ምክክር አድርገዋል :: ስብሰባው በኖርዌይ የስደተተኛ ማህበር የተዘጋጀ ሲሆን በስብሰባው  ላይ ከተለያዩ ከተሞች የመጡ እና በኦስሎ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች የተሳተፉ ሲሆን የኢሳት ጋዜጠኛ የሆኑት ጋዜጠኛ መታሰቢያ ቀፀላ እና ጋዜጠኛ ደረጀ ሃብተወልድ ጋር በመሆን በኖርዌይ ያሉ የኢትዮጵያውያን ስደተኞችን የአኗኗር ሁኔታ እንዲሁም ለስደት ያበቋቸውን ምክንያቶች በተመለከተ ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል፥፥

   በስብሰባውም ኢትዮጵያኖች በሀገራቸው እንዳይኖሩ የወያኔ መንግስት በሚያደርስባቸው ጫና እና በደል ሀገራቸውን ጥለው ቢሰደዱም ነገር ግን ኖርዌይ ከገቡ በኋላም የኖርዌይ መንግስት የኢትዮጵያኖችን የፓለቲካ ጥገኝነት በሚገባ እንደማያየው እና እንደማይቀበለው በየጊዜው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተለያየ ጫና እንደሚያደርስባቸው በሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን  በስብሰባው ላይ ከነበሩት ተሳታፊዎች የተለያዩ አስተያየቶች እና የየእራሳቸውን የህይወት ተሞክሮ እና ኖርዌይ ከገቡ ጀምሮ በሕይወታቸው ያለፈውን እና እየኖሩ ያለው ኑሮ ምን እንደሚመስል እንዲሁም ለስደት ያበቋቸውን ምክንያቶች በተመለከተ ውይይት አድርገዋል  ::

 አንዳንድ ሰዎች በተለያየ ምክንያት ከሀገር እየወጡ  ኖርዌይ ገብተው የፖለቲካ ጥገኝነት በመጠየቅ ወረቀት ካገኙ በኋላ ወይም ፖለቲካ ጥገኝነት ጠያቂ መስለው ትንሽ ጊዜ በመቆየት ካዛም በገዛ ፍቃዳቸው ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ እና  በኢትዮጵያ መንግስትም ምንም አይነት በደል እንዳልደረሰባቸው የኖርዌይ መንግስት እንደሚያውቅ ከዚህም የተነሳ ሌሎች ኢትዮጵያን ስደተኞ ላይ ወደ የፓለቲካ ጥገኝነት እንደማይቀበል ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱም የኖርዌይ መንግስት የተለያየ ጫና እንደሚያደርስባቸው በስብሰባው ከነበሩ ተሳታፊዎች የተገለጸ ሲሆን ነገር ግን  እንደነዚህ አይነት ሰዎች በመጀመሪያ ወደ ኖርዌይ የሚመጡበት ምክንያት እንዳላቸው እና ምክንያታቸውም  በኖርዌይ የሚኖሩትን እውነተኛ የወያኔ ተቃዋሚዎ ችን ለመሰለል እና ለማደን ሲሆን  እንደነዚህ አይነት ሰዎችን እንዳሉ እና እንደሚያውቆቸው ነገር ግን ኢትዮጵያውን እነዚህ የወያኔ ሰላዮች መፍራት እንደሌለባቸው ይህንንም ለኖርዌይ የስደተኞችን ጉዳይ ለሚመለከተው መስሪያ ቤት utlendingsnemnda (UNE) በተለያየ ጊዜ መሳወቃቸውን በስብሰባው ላይ ተገልጾል ::

በስብሰባው ላይ በመገኛት በኖርዌይ ያሉ የኢትዮጵያውያን ስደተኞችን የአኗኗር ሁኔታ ምን እንደሚመስል ጥያቄ ሲጠይቁት የነበሩት ጋዜጠኛ መታሰቢያ ቀፀላ እና ጋዜጠኛ ደረጀ ሃብተወልድ ኖርዌይ በሚኖሩት ኢትዮጵያኖች በሚያደርጉት ትግል ወይም እንቅስቃሴ በጣም እንደሚደሰቱ እና እንደሚደነቁ በመናገር ማንኛውንም ማድረግ ያለባቸውን እና ማድረግ የሚችሉትን  ነገሮች በማድረግ ከጎናቸው በመቆም አብራቸው እንደሚሰሩ ቃል ገብተውላቸዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዛሬው እለት ቅዳሜ የካቲት 22, 2006 ዓም በዛው በኖርዌይ ኦስሎ ኢሳት የእኔ ነው (ESAT IS MINE) በሚል መሪ ቃል የኢሳት ምሽት ፕሮግራም የተደረገ ሲሆን  የኢሳት ጋዜጠኛ የሆኑት ጋዜጠኛ መታሰቢያ ቀፀላ እና ጋዜጠኛ ደረጀ ሃብተወልድ የዝግጅቱ ተጋባዥ እንግዶች በመሆን በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተዋል ::

 በፕሮግራሙ የተለያየ ዝግጅቶች የተደረጉ ሲሆን በተለያዩ ሰዎች የኢትዮጵያን  የፖለቲካ ሁኔታ የሚዳስስ ጹሁፍ የቀረበ ሲሆን  ለኢትዮጵያ ህዝብ ያለምንም ፖለቲካዊ ወገንተኝነት መረጃን በማቅረብ ለኢትዮጵያ ሕዝብ አይን እና ጆሮ የሆነውን  ኢሳትን መርዳት እንደሚገባ በኖርዌይ የሚኖሩ የኢትዩጵያን ኮሚኒቲ ሊቀመንበር አቶ ፋሲል እና  የኢሳት ኖርዌይ ዋና ተወካይ ጋዜጠኛ አበበ ደመቀ  እንዲሁም በኖርዌይ የኢሳት ም/ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሙባረክ ንግግር አድርገዋል::በተጨማሪም አቶ እንግዳ ታደሰ የኢሳት በኖርዊይ አመሰራረት እና ስለ ኢሳት ባለቤትነት በህዝብ ዘንድ የሚወራው የተሳሰት ወሬ ትክክል እንዳልሆነ ኢሳት የማንም የፖለቲካ ድርጅት ንብረት እንዳልሆነ እና ኢሳት የኢትዮጵያ ሕዝብ ንብረት እንደሆነ ሕዝቡም ኢሳት የእኔ ነው በሚል ስሜት ኢሳትን እንዲረዳ እና እንዲደግፍ የኢሳትም አባል እንዲሆን ጥሪ በማቅረብ ንግግር አድርገዋል::


@በፕሮግራሙ ላይ የተለያዩ አስደሳች ግጥሞች እና መነባንቦች በተለያዩ ሰዎች የቀረበ ሲሆን በጋዜጠኛ ደረጀ ሃብተወልድ ኑ ሀገራችንን እንስራ በሚል ርዕስ ኢትዮጵያኖችን ለስደት የዳረገው ወያኔ በሰዎች ላይ የሚያደርሰው ግፍ እና በደል እንደሆነ እና  ስደት በሰው ሀገር  ምንም ቢመችም ደስታን እንደማይሰጥ የስደትን  ህይወት በሚመለከት አስደሳች እና ልብን የሚነካ ግጥም የቀረበ ሲሆን በጋዜጠኛ መታሰቢያ ቀፀላም ሁሉም ሰው የሀገሩ ሁኔታ ግድ እንዲለው እና ስለ ሀገር መቆርቆር ፣ሀገርን በሚመለከት ጉዳይ ላይ መሳተፍ  ፖለቲከኛ መሆን እንዳይደለ ሀገራችን ከወያኔ ስርዓት ነጻ እስከምትሆን ሁሉም ሰው በጽናት መታገል እንደሚገባው አጽንኦት ሰጥታ ንግግር ያደረገች ሲሆን በስብሰባው ላይ ዋናው አላማ የነበረው ማንኛውም ሰው ኢሳት የእኔ ነው በሚል ቃል በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች የኢሳት የባለቤትነት ስሜት ተሰምቷቸው ኢሳትን እንዲረዱ ከመሆኑ አኳያ በፕሮግራሙ ላይ ሲተላለፉ የነበሩት ግጥምም ሆነ ንግግር በዋናነት ኢሳት በመርዳት ላይ ያተኮረ ነበር :: በእለቱ የፕሮግራሙ አላማ የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ የጨረታ ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን በእለቱ ለኢሳት ማጠናከሪያ የሚሆን የተለያዩ ምግቦች ፣መጠጦች፣ ቀለበቶች፣እና ቲሸርቶች ለሽያጭ ቀርበዋል :: በተለያየ ጊዜ ለኢሳት እና ለፖለቲካ ድርጅቶች በሚደረጉ የገንዘብ ገቢ ማሰባሠቢያ ፕሮግራም ላይ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች ከየትኛውም ሀገር በበለጠ ንቁ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ይታወቃል::

tirsdag 17. februar 2015

Addisua Ethiopia : የ2007ቱን ሀገራዊ ምርጫ ሂደት እና ከምርጫዉ ዉጭ ያሉ አዋጭ አማራጮችን በተመ...

Addisua Ethiopia : የ2007ቱን ሀገራዊ ምርጫ ሂደት እና ከምርጫዉ ዉጭ ያሉ አዋጭ አማራጮችን በተመ...: February 14, 2015 | Filed under G7 Editorial , አማርኛ | Posted by admin አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ሕዝ...

የ2007ቱን ሀገራዊ ምርጫ ሂደት እና ከምርጫዉ ዉጭ ያሉ አዋጭ አማራጮችን በተመለከተ የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የአቋም መግለጫ

Addisua Ethiopia : የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ

Addisua Ethiopia : የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ: ጥር ፳፮(ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም :-<<ብሄራዊ ምርጫ ቦርድና ኢህአዴግ በወሰኑብን ፖለቲካዊ ውሳኔ ምክንያት አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ተነጥቀናል>...

የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ


የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ ጥር ፳፮(ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም :-<<ብሄራዊ ምርጫ ቦርድና ኢህአዴግ በወሰኑብን ፖለቲካዊ ውሳኔ ምክንያት አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ተነጥቀናል>> ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት› በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን ሰማያዊ ፓርቲ አስታውቋል፡፡ በእነ በላይ ፍቃዱ አመራርነት አንድነት ፓርቲን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ሲመሩ የነበሩ አመራሮች ዛሬ ጥር 26 ቀን 2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ፤ ከቀድሞ ፓርቲያቸው አንድነት ጋር የፕሮግራምም ሆነ የስትራቴጂ ተመሳሳይነት ወዳለው ሰማያዊ ፓርቲ ተቀላቅለው ሰላማዊ ትግላቸውን ለመቀጠል መወሰናቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
ሌሎችን የ አንድነት አባላትን በመወከል  መግለጫውን የሰጡት፦ የቀድሞው አንድነት ፓርቲ አፈ ጉባዔ  አቶ አበበ አካሉ፣ ምክትል አፈ ጉባዔ አቶ ፀጋዬ አላምረው፣ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ነገሰ ተፋረደኝ እና የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ናቸው፡፡
‹‹የምናምነው በሰላማዊ ትግል ብቻ ነው፡፡ ይህን ሰላማዊ ትግል ለመምራት ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ብቁ ነው ብለን በማመን ፓርቲውን ተቀላቅለናል›› ብለዋል የቀድሞዎቹ የአንድነት አመራሮች።  በዚህም መሰረት በርከት ያሉ  የአንድነት አመራሮችና አባላት በይፋ የሰማያዊ ፓርቲን የአባልነት ፎርም መሙላታቸው ተመልክቷል፡፡
በሌላ በኩል የአንድነት አባላት ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን አስመልክቶ መግለጫ ለመስጠት ወደ ሰማያዊ ቢሮ ባቀኑበት ወቅት ፖሊስ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ድረስ በመግባት፦ ‹‹በሰማያዊ ስም መግለጫ የሚሰጡ አካላት እንዳሉ ሰለሰማን ነው›› በሚል ለፓርቲው አመራሮች ጥያቄዎችን ማቅረባቸውን ከሰማያዊ ፓርቲ ጽህፈት ቤት የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።፡፡ ይህ  በእንዲህ እንዳለ-“በመድብለ ፓርቲ ስርዓት ስልጣን ይያዛል ብሎ ማመን ህዝቡን ማታለል ነው” ሲል አንድነት ፓርቲ አስታወቀ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ባወጣው መግለጫ  ስርዓቱ ለመድብለ ፓርቲ ፖለቲካ የሚመች የአስተሳሰብ ለውጥ እስካላመጣ ድረስ ፣ በመድብለ ፓርቲ ስርዓት ስልጣን ይያዛል ብሎ ማመን ህዝቡን ማታለል ነው ብሎአል።  የምርጫ ቦርድ ፓርቲውን ለማፍረስ የወሰደውን እርምጃ አጥብቆ የኮነነው አንድነት፣ አሁን ባለው ሁኔታ የመድብለ ፓርቲ ፖለቲካ ተቀበረዋል የሚል ድምዳሜ ላይ  መድረሱን አስታውቋል።  አባሎቹ ይህን ህገወጥ እርምጃ በፅኑ እየተቃወሙ ለነፃነትና ለኢትዮጵያዊነት የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመከፍል ዝግጁ መሆን እንደሚኖርባቸው አሳስቧል፡፡  ምርጫን በተመለከተ ፓርቲው አቋሙን ሲገልጽ፣ በአምስት ዓመት የሚደረግ ክብረ በዓል አድርጎ ለማድመቅ እና የህዝብ ሀብት ለማባከን በሚደረግ ሂደት ተሳታፊ ለመሆን አዲስ ፓርቲ መመስረትም ሆነ አሁን ካሉት ፓርቲዎች ጋር ተቀላቅሎ መታገል የሚያመጣው ለውጥ የለም ብሎአል፡፡ በመድብለ ፓርቲ ሰርዓት ስልጣን ይያዛል ብሎ ማመን ህዝቡን ማታለል ነው የሚል ፅኑ እምነት መያዙን የሚገልጸው አንድነት፣   የፓርቲ ፖለቲካ አላበቃም ብለው የሚያምኑ የአንድነት አባላት ካሉ በራሳቸው ነፃ ውሳኔ ወደ ፈለጉት ፓርቲ ተቀላቅለው የመታግል መብታቸው መጠበቁንም አስታውሷል።  ህዝቡ የትግሉ ባለቤት ሆኖ የስርዓት ለውጥ እንዲመጣ  የፓርቲው አባላት ሀገራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ቁርጠኞች መሆናቸውንም መግለጫው ጠቅሷል። አንድነት ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ውሳኔ እንዲፈርስ መደረጉ ብዙ ኢትዮጵያውያንን አበሳጭቷል።

5 የአየር ሃይል የጥበቃ አባላትና 2 ፓይለቶች ጠፉ

5 የአየር ሃይል የጥበቃ አባላትና 2 ፓይለቶች ጠፉ
Feb 06, 2015
ጥር ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአየር ሃይል ምንጮች እንደገለጹት ከሁለት ሳምንት በፊት 5 የአየር ሃይል የጥበቃ አባላት እስከነ ሙሉ ትጥቃቸው እንዲሁም 2 ፓይለቶች ከድሬዳዋ አየር ሃይል ጠፍተዋል። የጥበቃ አባላቱም ሆነ ፓይለቶቹ  ያሉበትን ለማወቅ የተደረገው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። ይህንን ተከትሎ ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ከመቶ አለቃ ማእረግ በላይ ያላቸውን አየር ሃይል አባላት ሰብስበው ግምገማ አካሂደው ነበር።
ጄ/ል ሳሞራ “የአየር ሃይል አባላት ለምን ይከዳሉ? አሁን ያላችሁትስ ምን ታስባላችሁ?” የሚል ጥያቄ ለተሰብሳቢው ያቀረቡ ሲሆን፣  የአየር ሃይል አባላቱም ከፍተኛ የሆነ የአስተዳደር በደል እንደሚደርስባቸው፣ ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ክፍያ እንደሚከፈላቸው፣ በመኖሪያ ቤት እጦት እንደሚሰቃዩ ገልጸዋል። መኮንኖቹ በርካታ ችግሮችን ዘርዝረው ያቀረቡ ቢሆንም፣ ጄ/ል ሳሞራ ችግሮችን ከመስማት ውጭ ምንም አይነት ምላሽ ሳይሰጡ ሄደዋል።

The 60th Birthday celebration of Andargachew Tesige in Oslo Norway

Posted: 15 Feb 2015 01:40 PM PS
On february 14.2015 was a big day for DECSON celebrating our Hero Andargachew Tesige 60th birthday prepared by  (Democratic Change in Ethiopia Support Organization Norway)
92 milio  -4miliio  banda  88miloions Ethiopians  we are Andargachew  .


As its known its has been almost 8 month since the brave hero and freedom fighter Andrgachew Tsgi has been kidnapped and arrested by the criminal regim TPLF.

Andargachew Tsige, secretary-general of Ginbot 7 has been labelled as a terrorist and labelled as working in a terrorist organisation by the Ethiopian government) only because He and his organization movement is a threat to the regime.

The 60th birthday celebration of Andargachew Tsige was world wide and here in Oslo celebrated  with warm cermoney presented about Andargachew’s  previous life history in a projector, like his educational background, where  he studys and also his struggle for freedom.
In additional there was a poem and birthday song.
Their was an invited gusts out of Norway who attend the celebration. People who love him and knows him were presented a speech about his patriotism and honest struggle. They called Him a true Ethiopian and the father of Ethiopians.
We Ethiopians can learn from Andargachew Tsige that freedom can not come without struggle and sacrifice.
Even though he is facing hard time in  Ethiopia he is remebered by the people who cares about him and will never stop pressing for his release until justice is served.
Hi is our hero and symbol of struggle that shows us commitment,devotion who cares for his motherland over his family. who never deserve to be in prison instead he deserves rewards for heroism.
Related Posts:

mandag 16. februar 2015

ሰበር ዜና – ምርጫ ቦርድ ሰማያዊ ፓርቲን ከምርጫ ለማገድ ፍላጎት እንዳለው ታወቀ፣ ‹‹ሰማያዊ ሳይጠብቁት በመላ አገሪቱ ዕጩ በማቅረቡ ደንግጠዋል›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

      February 15, 2015
• ‹‹ሰማያዊ ሳይጠብቁት በመላ አገሪቱ ዕጩ በማቅረቡ ደንግጠዋል›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
(ነገረ-ኢትዮጵያ) ምርጫ ቦርድ በየወረዳው ለሚገኙ የምርጫ ቦርድ አስፈፃሚዎች ‹‹ከቦርድ የሚጠበቅ ውሳኔ ስላለ፣ ሰኞ ተሰብስበን እስክንወስን ድረስ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎቹን ወደ ቅጽ 4 እንዳታዘዋውሩ›› የሚል መልዕክት ማስተላለፉን እና ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረባቸውን ዕጩዎች ከመቀነስ ጀምሮ ፓርቲውን ከምርጫው ለማገድ ፍላጎት እንዳለው ከምርጫ አስፈጻሚዎች መረጃዎች ደርሰውናል ሲሉ የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ፓርቲው ከትግራይ፣ እስከ ሞያሌ ጫፍ ዕጩ ማቅረቡ ለገዥው ፓርቲ ያልተጠበቀና አስደንጋጭ ሆኖበታል ያሉት ኢ/ር ይልቃል በህጋዊ መንገድ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ ላይ የሚደረጉት ጫናዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ሰማያዊ ሰይጠብቁት በመላ አገሪቱ ዕጩ በማቅረቡ ደንግጠዋል፡፡ በአዲስ አበባ 23 ዕጩዎችን አቅርበናል፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ አንድ ዕጩ ያቀረቡ ፓርቲዎች ሳይቀር በሚዲያ ሲነገርላቸው ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረባቸውን ዕጩዎች ለመግለጽ ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ ዛሬ ጠዋት ደግሞ የምርጫ ቦርድ ባለስልጣናት በቴሊቪዥን ቀርበው ‹ሰማያዊ በተደጋጋሚ ብንነግረው አልሰማም፣ በመሆኑም ሰኞ ቦርዱ ተሰብስቦ ውሳኔ ያስተላልፋል› ብለዋል፡፡ ይህም የሚያሳየው ሰማያዊ በምርጫው እንዳይሳተፍ ችግር መፍጠር እንደሚፈልጉ ነው፡፡›› ሲሉ ፓርቲው ላይ እየተፈጠረበት ያለውን ጫና ገልጸዋል፡፡
የምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ወንድሙ ጎላ በዛሬው ዕለት በኢቢሲ ቀርበው ሰማያዊ ይቅርታ ባለመጠየቁና ማስጠንቀቂያዎችን ባለመቀበሉ ነገ ሰኞ ጥር 9/2007 ዓ.ም ውሳኔ ያስተላልፋል ብለዋል፡፡
ከሌሎች ፓርቲዎች ሰማያዊን በመቀላቀል በፓርቲው ምልክት ለመወዳደር የወሰኑ ዕጩ ተወዳዳሪዎች እንዲሰረዙ መደረጉና በሌሎች ዕጩዎች ላይም ከፍተኛ ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ነገረ ኢትዮጵያ መዘገቧ ይታወሳል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን ፈረሲት ወረዳ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪ የሆነው አቶ ግርማ ቢተው በፈረሲት ወረዳ ፖሊሶች መያዙን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪዎች በገዥው ፓርቲ ደህንነቶችና ፖሊስ ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ተገልጾአል፡፡

በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ በወጣቶች ክፍል አስተባባሪነት በዛሬው እለት ሰኞ( January 26,2015) በኖርዌ ኦስሎ በእንግሊዝ ኢንባሲ ፊት ለፊት በኖርዌይ የሚኖሩ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በህብረት ሁነው ከ14፡00 _15፡00 ስዓት ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፉ በደማቅ ሁኔታ አካሄዱ።
የሰልፉ ዋና አላማ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሃፊ የነበሩትንና የሰባዊ መብት ተቆርቋሪ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በአረመኔው፣ ሰው በላ፣ ጨቋኙና በአንምባ ገነኑ የወያኔ ፋሺስታዊ ቡድን የአለም አቀፍ የሰባዊ መብትን ህግ በጣሰ መንገድ በሰኔ 2014 ታፍነው እስኳሁንም ድረስ ፍትህ ተነፍገው በእስር ቤት መታሰራቸውን ለመቃወም እንዲሁም የእንግሊዝ መንግስት አርበኛው የነጻነት ታጋዩ አንዳርጋቸው እየተፈጸመበት ያለውን ተፈጥሮአዊና ዲሞክራሲያዊ የመብት ጥሰት ተመልክቶ ከእስር ሊወጣበት የሚችልበትን አፋጣኝ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስዱ ለማሳሰብ ነው። 


በተጨማሪም አንዳርጋቸው ከተያዘበት ቀን ጀምሮ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በወያኔ የተፈጸመውን የውንብድና ድርጊት በመቃዎም ለእንግሊዝ መንግሥት በተለያየ መልኩ የአገሩን ዜጋ ህይወት ይታደግ ዘንድ በተደጋጋሚ ለማሳሰብ ቢሞከርም አፋጣኝ እርምጃ አለመወሰዱ ብዙዎችን አስቆጥቷል።
አንዳርጋቸው አገር ወዳድ፣ ሰላም ፈላጊ፣ ነጻነትና ፍትህ ናፋቂ፣ ለህዝብና ለአገር ክብር ተቆርቋሪ፣ ከእራሱ እና ከሚወዳቸው ቤተሰቦቹ ይልቅ ለእናት አገሩ ኢትዮጵያ ጊዜውን፣ እውቀቱንና ህይወቱን የሰዋ ብርቅዬ የኢትዮጵያ ጀግና መሆኑን በኩራት መስክረዋል። የውጭ ዜጎችም ሳይቀሩ ኢትዮጵያዊ ማንዴላ ብለው ሰይመውታል። ለዲሞክራሲ መከበር ለሚታገል አርበኛ እስርና እንግልት ኮቶ እንደማይገባ በተለይ የእንግሊዝ መንግሥት በትኩረት ሊመክርበት የሚገባ አንገብጋቢ ጉዳይ መሆኑን እና በወያኔ ላይ ግፊትና ጫና መፍጠር እንዳለበት ሁሉም ተሰላፊዎች ድምጻቸውን ከፍ አድርገው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።


እንዲሁም ሰልፈኞቹ የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ በታላቅ ድምጽና ስሜት የኖርዌይ ቅዝቃዜና በረዶ ሳይበግራቸው ለኢንባሲው አሰምተዋል። ከአሰሟቸው መፈክሮች መካከል ለአብነት ፣ “Andargachew is a freedom fithter, UK, were is your citizen, Free Andrgachew Tsige, Andargachew is our icon of democracy, where is your action , stop discrimination among citizens, Yes, we are all Andrgachew Tsige, Yes, Andargachew is an Ethiopian Mandela, Brtain don't support terrirost regim in Ethiopia, ” የሚሉት ይገኙበታል::
እንደተለመደው በድርጅቱ የተዘጋጀውን ደብዳቤ በድርጅቱ ተወካዮች በአቶ ይበልጣል ጋሹ እና በአቶ ዮናስ ዮሴፍ አማካኝነት ለእንግሊዝ ኢምባሲ ተወካይ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳዩ ትኩረት የሚሻና ጊዜ የማይሰጠው መሆኑን በመግለጽ ህይወቱም በእጅጉ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንዳለ በጥብቅ በማሳሰብ ደብዳቤውን በኢምባሲው ተወካይ አማካኝነት እንዲደርሳቸው ተደርጓል። 


በመጨረሻም ግፈኛው የወያኔ ቡድን በለመደው ተራ የሀሰት ወሬ በሚያወራበት ቴሌቪዥኑ ላይ ለትርጉም በሚያስቸግር መልኩ ቆራርጦና በጣጥሶ አንዳርጋቸውን ለማስወራት መሞከሩ የወያኔን ከንቱነት እና እውቀት ዓልባነቱ እንዲሁም ለህዝብና ለአገር የሚሰጠው ንቀት ይበልጥ ለዓለም መጋለጡ ለእኛ ለአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ህብርትና አንድነት ፈጥረን በእልህ፣ በቁጭትና በቁርጠኝነት ከበፊቱ በበለጠ ትግላችንን አጠናክረን እንድንቀጥል ትልቅ በር ከፍቶልናል፤ ለትግልና ለተቃውሞም ይበልጥ አነሳስቶናል። እንደ አርበኞችና ግንቦት ሰባት የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶችም ውህደት ፈጥረው በሁለገብ ትግል ዘረኛው ወያኔን ለማስወገድ ቆርጠው እንዲነሱ የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ ዮሐንስ ዓለሙ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በተመሳሳይም የወጣቶች ክፍል ተወካይ አቶ ይበልጣል ጋሹ ወጣቶች ለፍትህ፣ ለነጻነትና ዲሞክራሲ ለሚደረገው ትግል አስትዋጾ ማድረግ እንዳለባቸው በአጽንኦት አሳስበዋል።
ወጣት ሁሉን ነገር የመለወጥ ኃይልና አቅም አለው!አምባገነን መንግሥትን ማስወገድ እንችላለን! ወያኔን ከኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ማስወገድ እንችላለን!
ዛሬም ነገም ሁላችንም አንዳርጋቸው ፅጌ ነን!!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
የወጣቶች ክፍል