lørdag 29. juni 2013

ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

የትግራይ ህዝብ ነፃ ኣውጭ ድርጅት (ት. ህ. ነ .ኣ. ድ) በየካቲት ወር 1968 ዓ.ም ባወጣው የመጀመሪያ ዕትም መፅሔት ላይ ዐማራ የትግራይ ህዝብ ቀንደኛ ጠላት ነው በማለት የፖለቲካ አቋሙን ግልጽ አድርጓል። በዚህ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ግለሰብ ደግሞ ዓለምሰገድ ዓባይ ይባላል፤በትግራይ ክልል ውስጥ ባደረገው ጥናት 82 በመቶ የሚሆኑ የትግራይ ተወላጆች ተጀምሮ እስኪያልቅ ዐማራ የትግራይ ህዝብ ጠላት ነው ማለትን በጥናቱ ማጠቃለያ ላይ አረጋግጧል። በትናንትናው ዕለት ትግራይ ኦንላይ የተሰኘው የትግሬዎች ድረገጽ በአሁኑ ሰዓት በአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጽዳት ዘመቻ ተገቢ ነው በማለት በጥላቻ የተሞላ ግልጽ አቋሙን አሳውቋል። ይህ ደግሞ በዐማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጽዳት ዘመቻ ብዙዎች እንደሚሉት በሌሎች ኢትዮጵያውያን ላይ እንደሚፈጸመው ዓይነት አጠቃላይ የሰብዓዊ መብት ረገጣና የመልካም አስተዳደር እጦት አለመሆኑን በግልጽ ያሳያል። ጉዳዩ የመንግስትን ስልጣን በጨበጡ በወያኔ ትግሬዎች የሚፈጸም ሥር የሰደደ ጥላቻና በአንድ ዘር ላይ ያነጣጠር ጥቃት በመሆኑ ሁሉም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ በረጋና በሰከነ መንፈስ ሊመለከተው ይገባል። ያማራ ድምፅ እንደ አንድ ሀላፊነት የሚሰማው ዜጋ ያለምን ማቅማማት በትግራይ ነፃ አውጭዎች እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በተጭባጭ ማስረጃ አስደግፎ ለኢትዮጵያ ለህዝብ ያሳውቃል። እርሶም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ የሚችሉትን በማድረግ በሀገራችን ላይ ያንዣበበውን ጥፋትና ወደ እርስ በእርስ ጦርነት ሊያመራ የሚችል አደጋ በመከላከል የዜግነት ግዴታችንን በጋር እንወጣ።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar