lørdag 29. juni 2013

ሐረርነት እና ጎንደርነት! በሰሎሞን ተሰማ ጂ.

አዳላህ እንዳልባል እንጂ፣ የዚህ መጣጥፍ ርዕስ “ጎንደርነት እና ሐረርነት”ም ቢባል አያወዛግብም፡፡ ነገር ግን፣ ሐረር ከጎንደር በምስረታዋም ሆነ በቀደምትነቷ የታወቀች ስለሆነ ነው ርዕሳችንን ሐረርነት እና ጎንደርነት ያልነው፡፡ እንደምታውቁት ስለሐረርነት እና ስለጎንደርነት ማውራት ማለት፣ ስለሐረሬዎች ወይም ስለሐረሪዎች ማውራት አይደለም፡፡ በተመሳሳይ መልኩም፣ ስለጎንደርነት ማውራት ማለት፣ ስለጎንደሬዎች ማውራት ማለት አይደለም፡፡ የዛሬዎቹ ሐረሬዎችም ሆኑ የዛሬዎቹ ጎንደሬዎች ከመፈጠራቸው ብዙ መቶ አመታት በፊትም ሐረርነት እና ጎንደርነት ነበሩ፡፡ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ልናወሳው የፈለግነው ስለሁለቱ ከተሞች ሳይሆን ስለታሪካቸው፣ ስለስነ-ሰብዓቸው፣ ስለሃይማኖታቸው፣ ስለፖለቲካቸው፣ ኤኮኖሚያቸውና ስለባሕላቸው ነው፡፡ በጥቅሉ ይህ፣ ጽሑፍ የሐረር እና የጎንደር (ወይም አዳላችሁ እንዳንባል የጎንደር እና የሐረር) ፖለቲካዊ ፍልስፍናን በደሕና መስኮት ወደውስጣቸው ለማሳየት የሚጥር ይሆናል፡፡ (በበሩ ገብቶ ሐረርነትን እና ጎንደርነትን በቅጡ ማወቅ የሚፈልግ ካለ፣ ጠቀም ያለ ገንዘብ ቆጥቦ/ቋጥሮ ለቀናት ወይም ለወራት ያህል ቢጎበኛቸውና ቢያጠናቸው ይበጃል፡፡) ሐረርነት እና ጎንደርነት ብዙ-ብዙ ምስጢራትን የተሸከሙ ጽንሰ-ሃሳቦች ናቸው፡፡

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar