fredag 15. februar 2013

ፍቅርና አንድነት ያለው ህዝብ ጠላቱን ያሸንፋል


Posted: 11 Feb 2013 05:18 AM PST
    
ሉሉ ከበደ
ባለፈው ሂትለርና የወያኔን መሪዎች ባነጻጸርኩበት ጽሁፍ ላይ መለስ ስብሀት በአማራው ህዝብ ላይ በሰፊው ሊያንቀሳቅሱ የሞከሩት እልቂት አንዴት በሚፈልጉት ልክ እንዳልገፋላቸው ሗላ ላይ እናወጋለን ብየ ነበር።
በአለማችን ያሉ ጤናማ መንግስታት በዜጎቻቸው መካከል የመብት ልዩነትና የዘር የቀለም መለያየት፤ ግጭት እንዳይኖር ያለመታከት ይሰራሉ። ይተጋሉ። በኢትዮጵያ ያለው የዲያቢሎሶች መንግስት፤ ሰው በዘሩ ተለይቶ እንዲታወቅ፤ እንዳይስማማም እንዲበላላም ለማድረግ በትጋት ሲሰራ ሀያ ሁለት አመታትን አስቆጠረ።

ስርአትን መቃወም አንድ ነገር ነው።ስርአቱን ወደ ጎን አድርጎ አንድን ክፍለ ህዝብ እንደስርአት ስሎ፤ የመደብ ጠላት አድርጎ፤ አእላፍ ቋንቋ የሚናገርን ሕዝብ ለድህነትህ፤ ለሗላቀርነትህ፤ ተጠያቂ፤ ጠላትህ፤ ያንን ቋንቋ የሚናገረው ዘር ነው ብሎ፤ ባንድ ወገን ላይ የጥላቻ ዘመቻ ማንቀሳቀስ ዘርን ለማጽዳት ከሚደረግ ትልምና እቅድ የተለየ አላማ አለው ማለት ያስቸግራል።

ገዢ መደቦች ለፈጠሩት ስህተት ወይም ወንጀል፤ እነዚያ ገዢዎች የወጡበት ክፍለ ህዝብ እንደ ጠላት ተቆጥሮ ትውልድ በማያቀው ጉዳይና በማይደግፈው ድርጊት እዳ የሚከፍልበት አንዳችም ምክንያት አይኖርም። ባለፉት ሀያ ሁለት አመታት የህውሀት መሪዎች ስልጣኑን በጠመንጃ ተቆጣጥረው በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እያደረሱት ላለው በደልና ወንጀል፤ ለራሱም የችግሩ ሰለባ የሆነው የትግራይ ህዝብ ተጠያቂ ነው የሚል አስተሳሰብ ያለው፤ የሀያ አንደኛው ክፍለዘመን ኢትዮጵያዊ ይኖራል ብየ አላምንም። ምንጊዜም በሀገርና በህዝብ ላይ ለሚፈጸሙ አስተዳደራዊ ወንጀሎች፤ ተጠያቂው በአፈሙዝም ይሁን በምርጫ ስልጣን የተረከበውን ቡድን በበላይነት የሚመሩት፤ የህጉም የፖሊሲውም፤ አውጪዎችና አስፈጻሚዎች በጣት የሚቆጠሩት መሪዎች ናቸው እንጂ፤ ያመሪ የወጣበት የህብረተሰብ ክፍል አይደለም። በተዋረድ እንደየስልጣን ደረጃቸውና ሀላፊነታቸው እስከታች አርከን የወንጀሉ ተሳታፊዎች በህግ ይጠየቃሉ። ሕዝብ ከደሙ ንጹህ ነው።

1983 ወደ ሗላ መለስ ብየ ልጀምረውና በአርሲ አርባ ጉጉ፤ በአሰቦት ደብረወገግ ገዳም፤ በበደኖ፤ እና በሌሎቹም አካባቢዎች ህውሀት ወደ ስልጣን አንደመጣ በአማሮች ላይ ሊያንቀሳቅስ የሞከረው ፍጅት የተፈለገውን ያህል ውጤት ሊያመጣ ያልቻለው፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ለምእተ አመት ያካበተው ውህደት የፈጠረው፤ የወንድማማችነትና የአንድነት መንፈስ፤ አሸናፊ ሆኖ በመገኘቱ፤ ህብረተሰቡ ለዚያ መተላለቅ በቀላሉ ተነሳስቶ እነ መለስ ስብሀት ሚፈልጉትን ባለማድረጉ ነበር። ሌላው ምክንያት ታላቁ ያገር ልጅ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የመሩት እንባ ጠባቂ የመላው አማራ ህዝብ ድርጅት፤ በዚህ ክፍለ ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን ሰቆቃና በደል፤ ወያኔ ይዞት የመጣውን የዘር ማጥፋት እቅድ፤ በያለሙ እንዲስተጋባ በማድረጉ፤ አሁን ያለው የአለም ተጨባጭ ሁኔታ ያንን ሊያስቀጥል የሚችል አለመሆኑን ጌቶቻቸው ስለ ነገሯቸው ሊቀጥሉበት አልቻሉም።

ወደ መጀመሪያው ሙከራቸው ልሂድና የመጀመሪያውን እልቂት ሊያንቀሳቅሱ የሞከሩት የህውሀትንና የኦነግ ወታደራዊ ካድሬዎችን በማሰማራት ነበር። ህውሀትና ኦነግ ያሰማሯቸው የሁለቱ ቡድን መልከተኞች ናቸው አንጂ በአርሲም በሀረርጌም ያን መተላለቅ የፈጠሩት አብሮ የሚኖረው ህብረተሰብ አልነበረም።
ለዚህም ማስረጃ በወቅቱ እዚያው አካባቢ ስለነበርን ሀረርጌ በአካል ህብረተሰቡ ውስጥ ተገኝተን በተለይም ህውሀት ግጭቱን ለማንቀሳቀስ ኢላማ ያደረጋቸው አማሮችና ኦሮሞዎች እንዴት በመተሳሰብ ያንን ሁኔታ እንዳሳለፉት እንድ ተጨባጭ ታሪክ አቀርባለሁ።

ሐረርጌ አንድ ገጠር አውራጃ ውስጥ አማሮች እየታደኑ በሚገደሉበት ሰሞን የህውሀትና የኦነግ ካድሬዎች ባንዲት ገበሬዎች መንደር አንዱን ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ ጎልማሳ በገዳይነት ሊመለምሉት እቤቱ ይመላለሳሉ። አስፈላጊ ነው ብለው ያመኑበትን የፖለቲካና የዘር ጥላቻ ትምህርት ለሳምንታት በቤቱ እየተመላለሱ ከሰጡት በሗላ መሳሪያ ያስታጥቁታል። ልብ ይሏል በዚያን ጊዜ እነሱን መቃወም የኦሮሞን ነጻነት መቃወም ተደርጎ እርምጃ ያስወስዳል። ያ ድሀ አርሶ አደር አስፈላጊው የፖለቲካ ትምህርትና መሳሪያ ከተሰጠው በሗላ የተነገረው ተልእኮ ባካባቢው የሚኖሩ አማሮችን ስለሚያውቅ እያደነ እራሱ እንዲገድል ነበር።እዚያው አጠገቡ አብሮ አደግ ጉረቤቱ የሆነ ሰው ይኖር ስለነበረ ሄዶ እንዲገለው ትዛዝ ይሰጠዋል።

 ይህን ብለውት ከቤት እንደወጡ እሱም አብሮ ይወጣና ቆይቶ ወደቤቱ ተመልሶ ይመጣል። ከሰአታት በሗላ ተመልሰው ግዳጁን ተወቶ እንደሆነ ይጠይቁታል። እቤቱ የለም ይላቸዋል። አብሮ አደግ ጎረቤቱ ግን ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር እሳት ዳር ቁጭ ብለው ይጫወቱ ነበር። እነዛ የኦነግ እና የህውሀት አረመኔዎች ሲመጣ ጠብቆ እንዲገለውና ሪፖርት እንዲያደርግ ማስጠንቀቂያም ጭምር ሰተውት ይሄዳሉ። አሁንም ይህ አርሶ አደር ከቤት ወቶ እነሱ ሲሄዱ ተመልሶ ከቤቱ ይቀመጣል። በድጋሜ ተመልሰው መጡና ትዛዛቸው መፈጸሙን ሊያረጋግጡ “ገደልከው?” አሉት።

ያ ቅዱስ የኦሮሞ አርሶ አደር እንባውን እያፈሰሰ “…እባካችሁ ተውኝ .. ይህን ድሀ አብሮ አደግ ወንድሜን ግደል አትበሉኝ ። ይህንን የኔቢጤ ሚስኪን ብገድለው ድህነቱና ቅማሉ አንጂ ምን ይተርፈኝ መሰላቸሁ። ግደሉኝ ብትፈልጉ… አልገለውም..፡ “ በማለት ያሸከሙትን መሳሪያ ወዲያ ወረወረው። እነዚያ ካድሬዎች ያንን ድሀ አማራ ያን እለት ከነልጆቹ ይዘውት ሄዱ። ወዴት እንዳደረሷቸው ግን አይታወቅም።

በዚያን ጊዜም ሆነ አሁን ከሀያ ሁለት አመታት በሗላ ወያኔዎችም ሆኑ የተወሰኑ ኦነጎች ችግራቸው ለራሳቸው ተጭነውት የሚሰቃዩበትን በሽታ በቀጥታ በህብረተሰቡ ላይ ለማራገፍ ከመጣደፍ በቀር እዚያ የደረሱበት አካባቢም ሆነ በማናቸውም ጥግ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ “በእንዴት ያለ ሁኔታ ነው አብሮ መኖር የያዘው? ትስስሩና ፍቅሩ እምን ድረስ ነው? ውህደቱና ስምምነቱ እምንድረስ ነው ?” ብለው የህብረተሰቡን ሁኔታ ለማጥናት ጊዜ አይወስዱም። የኢትዮጵያ ህዝብ እነሱ በታወሩበት የዘረኝነት በሽታ ታውሮ የሚኖር ነበርም ነውም የሚመስላቸው።

በወቅቱ የታዘብኩትን ሌላ ገጠመኝ ላውጋ። እዚያው ሀረርጌ ውስጥ ነው። ጊዜዋም ያችው ቀውጢዋ ነበረች። አንዲት የወረዳ ከተማ ውስጥ ልዩ ልዩ ብሄረሰቦች ይኖራሉ። አብዛኛው ኦሮሞ ይሁን እንጂ አማራ፤ ጉራጌ፤ አፋር፤ከሶማሌ ብሄረሰብ ኢሳ የሚኖሩበት ከተማ ነች። እነዚህ ክፉ ሰዎች ገና ሁሉንም ተቆጣጥረው እንደጨረሱ ቢሆንም በደንብ አልተረጋጋም። ኦነጎችም እስር እስራቸው ይሉ ነበር። በዚች በማወሳት ትንሽ ከተማ ውስጥ አስተዳዳሪዎች ነን ብለው ኦነጎች ቢሮ ገባ ገባ ብለው የነበረበትና አለቆቻቸውም ከወያኔ ጋር ሽግግር ምክር ቤት ሽር ጉድ ይሉ የነበረ ጊዜ ነው። ክልሉ የኦሮሞ ስለሆነ እናስተዳድራለን ይሉን የነበሩት የኦነግ ታጣቂዎች አምስት ስድስት ትላልቅ የኝነት መኪና ሞልተው፤ ጠመንጃ ተሸክመው፤ ላይ ታች በከተማው ዥው ዥው ይሉ የነበሩቱ እያስተዳደርን ነው ብለው ቢሮ በገቡ በሶስተኛው ቀን፤ ኦሮምኛና ትግርኛ እንጂ አንዲት የአማርኛ ዘፈን እንዳንሰማ በማለት “ይህንን ግም አፍ” ከእንግዲህ ሲያዘፍን የተገኘ እርምጃ ይወሰድበታል ብለው ሖቴሎችና ሻይቤቶች ሳይቀሩ አማርኛ እንዳያዘፍኑ ትዛዝ አስተላለፉ። ጠቅላላው የከተማዩቱ ነዋሪ ፈራ። ወዲያው ደግሞ ቀጠሉና በአራተኛው ይሁን በአምስተኛው ቀን የአማርኛ ቋንቋ እንዳይነገር መመሪያ ሰጡ።


በዚህን ጊዜ ነው የከተማዩቱ ኦሮሞ ነዋሪዎች ከሌሎቹ ነዋሪዎች ጎን በመቆም “አይዞአችሁ። እነዚህ ኦሮሞዎች አይደሉም። ምን እንደሆኑም አናውቅም። ተረጋጉ ።” ብለው በቀጥታ ከነዚያ ሰዎች ጋር መላተም የጀመሩት። በከተማዩቱ የኢሳ ብሄረሰብም ይኖራል ብያለሁ። ለገበያ ይመላለስባታል። እነሱም ክልሉ የኛነው ይሉ ነበረና ይህ ሁሉ ሲሆን ለካንስ ኢሳዎች በጥሞና እየተከታተሉ “ምንድናቸው?” ብለው ይጠይቃሉ። “ኦነግ” ይሏቸዋል። “ኦነግ ምንድነው? ምን ያደርጋሉ እዚህ?” “የኦሮሞ ነጻ አውጭ ናቸው ያስተዳድራሉ” ተባሉ።

በመሰረቱ ከጥንት ጀምሮ የኢሳ ብሄረሰብና ኦሮሞ ይጣላሉ። ልማዳዊ አለመግባባት አለ። የኢሳ ብሄረሰብ ዘላን ከብት አርቢ ስለሆነ ሳር ፍለጋ ከብቶቹን ከቦታ ቦታ በሚያንቀሳቅስበት ጊዜ ኦሮሞዎች የሚኖሩበትንም አካባቢ መድረሱ ስለማይቀር፤ የተሰማሩ ከብቶችን ካገኘ እየቀማም እየዘረፈም ከመንጋው ቀላቅሎ ይዞ መሄድ የተለመደ ነገር ነው። ለማስመለስ መሳሪያ ሳይቀር ይመዘዛል። ሰውም ይሞታል።

እና ታዲያ አሁን በማወሳት ከተማ ውስጥ ሕዝቡን መከራ እያበሉ ያሉትን የኦነግ ተዋጊዎች “ይህ ክልሉ የኛ ስለሆነ ለቃችሁ ውጡ” ብለው ሽማግሌ ይልኩባቸዋል። ጌታዋን የተማመነች በግ ላቷን ደጅ ታሳድራለች እንደተባለው ወይም ወያኔ አለልን ብለው ወይም ደግሞ ኢሳ ተዋጊ መሆኑን አለማወቅ፤ ማስጠንቀቂያውን ከእቁብ ሳይቆጥሩ ሰዉን ማሸበራቸውን ቀጠሉ። በዚህን ጊዜ ኢሳ ጦርነት ሊከፍት ከየገጠሩ እየተጠራራ በከተማዩቱ ሰፍሯል። እነ ኦነግም በበርካታ የጭነት መኪኖች ሞልተው ላይ ታች ይላሉ። ጥቂት የወያኔ ወታደሮች ከተማው ጥግ ሰፍረው የሚሆነውን ይከታተላሉ። ጣልቃም አይገቡም።


አንድ ቀን ጠዋት ማለዳው ላይ ያቺ ትንሽ ከተማ በቀላል ነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያ ተኩስ ልትፈነዳ ደረሰች። ለሁለት ሰአት አካባቢ ሞቅ ያለ ተኩስ ከተሰማ በሗላ፤ መልሶ ጸጥ ለጥ ረጭ አለ። እስከቀትር ድረስ ሰውም ከቤት አልወጣ ከተማዋ ጭር እንዳለች ዋለና ሗላ ላይ የኢሳ ብሄረሰብ ወዲያ ወዲህ ሲል ሁላችንም ከተሸሸግንበት ወተን የሆነውን እናጠያይቅ ጀመር። አዎ እነዚያ ሰዉን ያምሱት የነበሩ የኦነግ ጂሎች መሬት ይግቡ ሰማይ የደረሱበት አይታወቅም። የሞተው ሞቶ የቀሩት ድራሻቸው ጠፍቷል። ወዲያውኑ በየሆቴሉ በየሻይቤቱ የአማርኛ ዘፈን ይሰማ ጀመር። ሰውም ጮክ ብሎ አማርኛ ያወራ ጀመር። የከተማዪቱ ኦሮሞኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች በዚያን ሰሞን ለቀረው ህዝብ ያሳዩት አጋርነትና ተቆርቋሪነት፤ ያሳዩት ወገንተኝነትና አብሮነት የዘር ድርጅት መሪዎች እጅግ ብዙ ሊማሩበት የሚያስችል ክስተት ነበር።

ታዲያ ግጭቱ ከተከሰተ በሗላ ምን ይሆን ትተው የሄዱት፤ በየቢሮው ጥለውት የሄዱ ሰነድ ካለ ምን ይሆን እቅዳቸው አልንና የተወሰንን ሰዎች በየቢሮው ገብተን መበርበር ጀመርን። ያገኘነው አስደንጋጭ ነገር ቢኖር በከተማዋ ነዋሪ የሆኑ፤ ነዋሪው በጠቅላላ የሚያከብራቸው፤ የሚወዳቸው፤ ያገር ሽማግሌዎች የሞተን የሚቀብሩ፤ የታመመን የሚያስታምሙ፤ የተቸገረን የሚረዱ፤ አስራ ስድስት ነዋሪዎች ስም ዝርዝር እንዲገደሉ በቃለጉባኤ ተፈርሞበት ተቀምጧል። ለኦሮሞ ህዝብ ነጻነት እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ነፍጠኞች ስምዝርዝር ይላል። የሚደንቀው ደግሞ ከነዚያ ሰዎች አራቱ ኦሮሞዎች ነበሩ።

ያቺ የኢሳ ብሄረሰብ ያስነሳት አጭር ጦርነት የነዚያን ንጹሀን ዜጎች ህይወት ለማትረፍ በቃች።ሕህቡንም ከመራር ሀዘን አዳነችው።
የኢትዮጵያ ህዝብ እንደነዚህ አይነት በሽተኞችን ይዞ ነው የሚጓዘው። ይህ የዘር ጥላቻ፤ ይህ የዘር ፖለቲካ፤ የወያኔን መሪዎችና መሰሎቻቸውን ለጊዜው ተጠቃሚ ሊያደርጋቸው ይችላል። በረጅም ጊዜ ጦሱ ግን የሚያጠፋቸው ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ለዘመናት ያካባተው፤ ያዳበረው አብሮ የመኖር የአንድነትና የመተሳሰብ መንፈስና ባህል ምንጊዜም በውስጡ ያለ በመሆኑ አንድ ቀን እነዚህን የዘር ልክፍተኞች በቃችሁ እንደሚላቸው ጥርጥር የለውም። የኢትዮጵያን ሀብት ዘርፈን የ ኢትዮጵያን ህዝብ በትነን የራሳችን መንግስት እናቆማለን ብለው ለሚቧችሩ ወዮ ለነሱ ይህ ሕዝብ አንድ ሆኖ በቃ ያለቀን።በመጨረሻዋ ሰአት ወዮ ለዘረኞች!
በስደት በምንኖርበት የባእድ አገር ጽንፈኛ የዘር ፖለቲካ አቀንቃኞች ለልጆቻቸው እንዴት ጥላቻን እንደሚያስተላልፉ የሚያመለክት አንድ ገጠመኝ ላክል።ይህንን ታሪክ ያጫወተኝ ሰው ነገሩ ለርሱ ብዙም ክብደት አልሰጠውም። የልጅ ነገር ብሎ እየሳቀ ነው የነገረኝ። እኔ ግን ከልጅ ነገርነቱ ባሻገር ነው የከፋ ነገር የታየኝ። ላንባቢያን ባካፍለው ሁላችንም እንማርበታለን ብየ አሰብኩ።


ሁለት ህጻናት ወንዶች ልጆች እድሜያቸው አስራ አንድ አመት የሆኑ ትምህርት ቤት ተከፍቶ አንድ ክፍል ይመደባሉ። ሁለቱም ኢትዮጵያውያን ናቸው። ያንኑ እለት በእፈፍት ሰአታቸው እግር ኳስ ሊጫወቱ እየተሯሯጡ ኳስ ሜዳ ገብተው ጥቂት እንደተጫወቱ ለማረፍ ወደሜዳው ጥግ ሄደው ሳር ላይ ቁጭ እንዳሉ ይተዋወቁና ጎን ለጎን ተንጋለው ወሬ ይጀምራሉ። ከየት እንደመጡ ይጠያየቃሉ። አንደኛው ከኢትዮጵያ አንደመጣ ሲነግረው ሌላኛው ከኦሮሚያ ነው የመጣሁት ይለዋል። ሁለቱም የኦሮሞ ብሄረሰብ ተወላጆች ናቸው። ይህ ከኢትዮጵያ ነው የመጣሁት የሚለው ልጅ “ ኦሮሚያ የት ነው” ይለዋል አዲሱ ጓደኛውን።
“ እሩቅ አፍሪካ ውስጥ ነው።” ይመልሳል የኦሮሚያው ልጅ
“ እዚህ አገር ከመጣህ ተመልሰህ ሄደሀል?”
“ አዎ ሰባት አመት የነበርኩ ጊዜ ሄጄ ነበር”
“ እኔም ስድስት አመት የነበርኩ ጊዜ አባቴ ወስዶኛል። ኢትዮጵያ ብዙ ደስ ብሎች አሳለፍኩ…ኦሮሚያ ከኢትዮጵያ በየት በኩል ነው?”
ተጠያቂው ህጻን ኦሮሚያ በየት በኩል ነው ለሚለው ጥያቄ መልስ ከመስጠቱ በፊት “አማራ ነህ?” ይለዋል። ከኢትዮጵያ መጣሁ የሚለው ልጅ ብሄሩንም አያውቅምና “ እኔ አንጃ “ ይላል።
ያም ቀበል ያደርግና “ ኢትዮጵያ የአማራዎች አገር ነው። ጥሩ አይደለም። ኦሮሚያ ጥሩ ነው። “ ይላል።

ብዙም አልተግባቡ ወደጨዋታቸው ይመለሳሉ። ይህ ከኢትዮጵያ ነው የመጣሁት የሚለው ልጅ ይህንን ታሪክ ለወላጆቹ ይነግርና “ኦሮሚያ የት ነው አዲስ ጓደኛ አገኘሁ” ይጠይቃል አባትን። አባትም ኦሮሚያ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ አንድ ክልል መሆኑን ያስረዳና የሚኖሩበት አገር ካናዳን እንደምሳሌ አድርጎ ፕሮቪንሶቹን እየጠራ እንደ አንዱ እንደማለት ነው ካለ በሗላ “ሁለታችሁም ኢትዮጵያውያን ናችሁ። ወንድማማቾች ናችሁ። ጥሩ ጓደኛ አግኝተሀል እንኳን ደስ ያለህ” ይለዋል።
ልጅ ይህንኑ ካባቱ የተነገረውን በሁለተኛው ቀን ትምህርት ቤት ሲሄድ ለአዲሱ ጓደኛው ያስረዳና በጓደኝነታቸው እንደሚቀጥሉ ይነግረዋል።

ያኛው ህጻን ግን ባልተጠበቀ መልኩ የሚያስከፋ መልስ ይሰጠዋል። “…ኖ!..ኖ! ከንግዲህ አንተ የኔ ጓደኛ አትሆንም አንተ….ነህ ..I hate…..” እያለ ጥሎት ይሄዳል።
በሁኔታው ግራ የተጋባው ልጅ እንደገና ይህንኑ ታሪክ ላባቱ ይወስድና አማራ ምንድነው? ብሎ ይጠይቃል። አባት ብዙ ዝርዝር ውስጥ ሊገባ አልፈለገም። “ ጓደኛ አልሆንህም ካለህ ምርጫውን አክብር። አትረብሸው። ሌላ ጊዜ በደንብ ስትተዋወቁ ጓደኛ ትሆናላችሁ “ በማለት ልጁን ያጽናናል።

ይህ ቡቃያ ከእናቱ ወይም ከአባቱ የዘር ፖለቲካ ልክፍተኛ እንዳለበት ምንም ጥርጥር የለውም። በዚህ መልኩ ነው የጥላቻ በሽታ ከቤተሰብ ወደ ልጆች የሚተላለፈው፤ የሚጋባው። አሁን በሀገራችን ስልጣኑን የተቆጣጠሩት የሕውሀት መሪዎች የዚህ አይነት አስተዳደግ ውጤቶች ናቸው ብየ ነው የማምነው።

መልካሙ ነገር እነዚህ ህጻናት እኛ ካደግንበት ወይም ሀገርቤት ያሉት ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው ከሚያድጉበት የተሻለ አለም ውስጥ ስለሆነያሉት፤ ነገ ጠዋት ሁላችንንም ወላጆችን እንደሚያርሙንና እንደሚተቹን የሚያጠራጥር ነገር የለውም፤ ምክንያቱም መንግስታቸው “በቆዳ ቀለምና በዘረኝነት አትታወር” እያለ ነውና የሚያሳድጋቸው።

በዛሬዪቱ ኢትዮጵያ በወያኔ ዘረኛ ገዢ ቡድን አስተዳደር ስር ያሉት ሕጻናቶቻችን አየሩ ሁሉ በዘር ፖለቲካ ሰበካ፤ በጥላቻ ወሬ፤ በልዩነት ፕሮፓጋንዳ ጩኸት በተወረረበት፤ ንጹህ አየር ተንፍሰው ለማደግ ፋታ ባጡበት ሁኔታ ሬዲዮ፤ ቴሌቪዥን ወያኔያዊ ሀሰተኛ የውንጀላ ድራማና ወሬ ብቻ በሆነበት ዘመን፤በሀሰት፤ በክህደት የሀገርን ታሪክ፤ የህዝብን አንድነት የሚያረክስ ሴጣናዊ ወያኔያዊ የቁራ ጩኸት ብቻ በሆነበት ምድራችን ለሚያድጉት ህጻናቶቻችን የወደፊት እጣፈንታ መጨነቅ ያስፈልገናል።

ባለፉተ ሀያ አመታት ውስጥ በሀገሪቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምናየው አንዳንድ ምልክት ወያኔ የዘራው በሽታ የሚፈልገውን ፍሬ እያፈራለት መሆኑን ያመለክታል። በዘር ተለያይተው የሚደባደቡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ ለማየት ችለናል። ነገ ሀገሪቱን የሚረከቡ ዜጎች ናቸው። ወያኔ እያሳየን ያለው ምን ያህል ትውልዱን እያዘቀጠልን እንዳለ ነው። ተበልጠናል። ልጆቻችንን ለወያኔ የዘረኝነት ፕሮፓጋንዳ ሰለባ ከመሆን ልናድናቸው አልቻልንም። አንድ ሆነው እንዲቆሙ ወላጆች ማስተማር አልቻልንም። ከህብረተሰብም ከትምህርትቤትም በፊት ሰው የሚቀረጸው በቤት ውስጥ ነው። ኢትዮጵያዊ ማንነታቸውን፤ ህብር ህዝብነታቸውን፤ የባህል የቋንቋ የስነልቡና ውህደታቸውን አያት ቅድም አያቶቻው ከባእዳን ወራሪዎች ጋር ተፋልመው ያቆዩአት አንዲት የጋራ ሀገር እንዳለቻቸው፤ ባለመጠራጠር እንዲያውቁ አላደረግንም። ለዚህም ነው ከአንድነታቸው ይልቅ ልዩነታቸው እየጎላ የታያቸው ልጆች ወያኔ መፍጠር የቻለው።ለዚህም ነው የወያኔን ሴራና ተንኮል መረዳት አቅቶአቸው አንዲህ ተባልን እንዲህ ሆን ብለው ሆብለው ለጅምላ ድብድብ መፍጠን የቻሉ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ማየት የቻልነው።

ለራሳችንም የዘር በሽታ ልክፍተኛ የሆን ወገኖች በሽታችንን፤ ህመማችንን፤ዋጥ አድርገን ለልጆቻችን ደግደጉን መንገር አልቻልንም።
የኢትዮጵያ ልጆች እጣ ፈንታ በኛ በወላጆቻቸው ትከሻ ላይ ነው ያለው አንጂ በመርዘኛው የወያኔ ገዢ ቡድን እጅ ውስጥ አይደለም። ወያኔ እየጋታቸው ያለውን የመጥፊያ መርዝ እንዳይውጡ ማድረግ የኛ ፋንታ ነው። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ወላጅ በቤቱ ውስጥ የኢትዮጵያዊያንን እኩልነት ብዛትና አይነት ባህላችንን ቋንቋችንን አንድነታችንን የምድራችንን ልክ ማስተማር ይጠበቅብናል።
ከውጭ ወራሪ ጠላት የከፋ ጠላት ከውስጥ ስለተቆጣጠረን፤ በዘር በሽታ የተለከፍን ሁሉ አማራውም፤ ኦሮሞውም፤ ትገሬውም፤ አፋሩም፤ ሶማሌውም…ሁሉም!…. ካባቶቻችን የወረስነው የመጠላላት በሽታ ካለ ዋጥ አድርገን፤ ነገ አብረው መኖር ስላለባቸው ልጆቻችን፤ ቡቃዮቻችን እናስብ።

የሚቀጥሉት ሰላሳና አርባ አመታት ነገሩ ሁሉ አሁን አንዳለው ከቀጠለ፤ልጆቻችን እርስበርስ ሲናቸፉ፤ ወያኔና ከውጭ በገፍ እያስገቡአቸው ያሉት ባእዳን ባለሀብቶች ይህችን ሀገር ይቆጣጠሯታል። ይቀራመቷቷል። እነዚህ ከውጭ እያስገቡ መሬት የሚያድሏቸው ባእዳን ሁሉም ሀብታምና ትልልቅ መንግስታት ከጀርባ አላቸው። ቻይና፤ ሳውዲአረቢያ፤ አሜሪካ፤ እንግሊዝ፤ ሕንድ፤ወዘተ…ለህዝባቸው የተትረፈረፈ ምግብ፤ ለኢንዱስትሪአቸው ጥሬ ሀብት፤ ለሸቀጣቸው ማራገፊያ ሰፊ ገበያ ኢትዮጵያ እየተበለተችላቸው ነው።

መሬትን ለማረስ መጀመሪያ ደኑን መመንጠር እንደሚገባ መሬቱን ለባእዳኑ ለመሸጥ መጀመሪያ ወያኔ ዜጎቻችንን በመግደል እየመነጠረ የሚሸጠውን ቦታ እያመቻቸላቸው ነው። በቅርቡ የሱሬ ብሄረሰቦች መቶ ሀምሳ የሚሆኑ ከመሬታቸው ከቀያቸው ውስጥ ተሰብስበው በመትረየስ ተጨፍጭፈው ተጥለዋል። አሁን መሬቱ ተመንጥሯል። ባእዳኑ ገንዘቡን ከፍለው መረከብ ይችላሉ።የኢትዮጵያ ህዝብ ምን አይነት የማደንዘዣ መርፌ እንደወጉት አይታወቅም፤ ተራ በተራ እየገደሉ እስኪጨርሱት ተቀምጦ እየጠበቃቸው ነው።

ዛሬ እንዲጠላሉ አድርገን ያሳደግናቸው ልጆቻችን ነገ ምድራቸውን የተቀራመቷት ባእዳንና ወያኔዎች በሚያቀርቡላቸው ጠመንጃ ስራቸው መዋጋት ይሆናል። የምድሪቱን ቱሩፋትና በረከት በብዙ ሺህ ማይልስ ርቀት ላይ ያሉ ህዝቦች ይኖሩበታል። በብዙ ሺህ ማይልስ ርቀት ላይ የሚገኙ የሀብታም ልጆች ይፋፉበታል ያድጉበታል። ይህችው ምድር ያበቀለቻቸው ዜጎቿ ያልታደሉቱ፤ ይራቡባታል። እርስበርስ እየተታኮሱ ይገዳደሉባታል።በወያኔና መሬቱን በተሸለሙት ሀብታም መንግስታት ወታደሮች ይገደሉባታል።

ልጆቻችንን ከመጠላላት ፖለቲካ እናድን። ለማናችንም አይበጅም። እኛም በሽታው ካለብን ዋጥ አናድርገው። ቀጠሮ የምንሰጠው ጉዳይ አይደለም። ዛሬ!..ዛሬ!..ዛሬ ነው ጊዜው። ፍቅርና አንድነት ያለው ህዝብ ያሸንፋል።የጋራ ጠላታችን ወያኔን አምርረን እንዋጋ።እርስበርስ መጠላለፉ እልቂታችንን ያቀርበዋል።ለመዳን አንድ እንሁን!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

Posted: 11 Feb 2013 04:43 AM PST
Ethiopia: Where Do We Go (or not go) From Here? 
by Alemayehu G. Mariam
 
For some time now, I have been heralding Ethiopia’s irreversible march from dictatorship to democracy. In April 2011, I wrote a commentary entitled, "
The Bridge on the Road(map) to Democracy". I suggested,

We can conceive of the transition from dictatorship to democracy as a metaphorical journey on the road to progress, freedom and human enlightenment (democracy) or a regression to tyranny, subjugation and bondage (dictatorship). Societies and nations move along this road in either direction. Dictatorships can be transformed into democracies and vice versa.

 But the transition takes place on a bridge that connects the road from dictatorship to democracy. It is on this bridge that the destinies of nations and societies, great and small, are made and unmade. If the transition on the bridge is orderly, purposeful and skillfully managed, then democracy could become a reality. If it is chaotic, contentious and combative, there will be no crossing the bridge, only pedaling backwards to dictatorship. My concern is what could happen on the bridge linking dictatorship to democracy in Ethiopia when that time comes to pass

In June 2012, I wrote a commentary entitled, "
Ethiopia: On the Road to Constitutional Democracy". I argued with supporting historical evidence that "Most societies that have sought to make a transition from tyranny and dictatorship to democracy have faced challenging and complex roadblocks." Focusing on the practical lessons of the "Arab Spring", I proposed a constitutional pre-dialogue and offered some suggestions:

The search for a democratic constitution and the goal of a constitutional democracy in Ethiopia will be a circuitous, arduous and challenging task. But it can be done… To overcome conflict and effect a peaceful transition, competing factions must work together, which requires the development of consensus on core values. Public civic education on a new constitution must be provided in the transitional period. Ethiopian political parties, organizations, leaders, scholars, human rights advocates and others should undertake a systematic program of public education and mobilization for democratization and transition to a genuine constitutional democracy. To have a successful transition from dictatorship to constitutional democracy, Ethiopians need to practice the arts of civil discourse and negotiations


They are pedaling backwards on the low road of dictatorship, but are we marching forward on the highway to democracy?


 
It is easy for some people to speak truth to power, or the powers that be. Without great difficulty, they can preach to abusers of power why they are wrong, what they are doing wrong, why they should right their wrong and do right by those they have wronged. But it is not so easy to speak truth to powers that could be, particularly when one does not know who "they" are. Instead of speaking truth to the powers that could be, I will simply ask: They are pedaling backwards on the low road of dictatorship, but are we marching forward on the highway to democracy? Where do we go (or not go) from here?

Ordinarily, this question would be put to Ethiopia’s "opposition leaders". For some time now, I have been wondering who those leaders are and are not. In my commentary last September entitled, "
Ethiopia’s Opposition at the Dawn of Democracy?", I asked out loud (but never got answer), "Who is the Ethiopian ‘opposition’?"

 
I confessed my bewilderment then as I do now: "There is certainly not a monolithic opposition in the form of a well-organized party. There is no strong and functional coalition of political parties that could effectively challenge both the power and ideology of the ruling party. There is not an opposition in the form of an organized vanguard of intellectuals. There is not an opposition composed of an aggregation of civil society institutions including unions and religious institutions, rights advocates and dissident groups. There is not an opposition in the form of popular mass based political or social movements. There is not…"

Stated differently, is the "opposition that amorphous aggregation of weak, divided, squabbling, factionalized and fragmented parties and groups that are constantly at each other’s throats? The grumbling aggregation of human rights advocates, civic society organizers, journalists and other media professionals and academics? The groups committed to armed struggle and toppling the dictatorship by force the opposition? Anyone who thinks or self-proclaims s/he is the opposition?" All or none of the above?

 
I am willing to bet my bottom dollar that the disciples of the late Meles Zenawi would have no problems explaining where they are going from here. They would state with certainty, "Come hell or high water, we’ll pedal backwards lockstep in Meles’ ‘eternally glorious’ footsteps to the end of the rainbow singing Kumbaya to grab the pot of gold he has left for us under the Grand Renaissance Dam. We will fly high in the sky on the wings of a 10, 12, 15 percent annual economic growth and keep flying higher and higher…" I say it is still better to have a road map to La-La Land than sitting idly by twiddling one’s thumbs about the motherland.

Is the question to be or not be in the opposition? What does it mean to be in the "opposition"? What must one do to be in the "opposition"? Is heaping insults, bellyaching, gnashing teeth and criticizing those abusing power the distinctive mark of being in the opposition? Is frothing at the mouth with words of anger and frustration proof of being the opposition? How about opposing the abusers of power for the sake of opposing them and proclaiming moral victory? Is opposing the abusers of power without a vision plan, a plan of action or a strategic plan really opposition?

 
I have often said that Meles believed he "knew the opposition better than the opposition knew itself." Meles literally laughed at his opposition. He considered the leaders of his opposition to be his intellectual inferiors. He believed he could outwit, outthink, outsmart, outplay, outfox and outmaneuver them all, save none, any day of the week. He believed them to be dysfunctional, shiftless and inconsequential; he never believed they could pose a challenge to his power.

In his speeches and public comments, he ridiculed, scorned and sneered at them. He treated his opposition like wayward children who needed constant supervision, discipline and well-timed spanking to keep them in line. Truth be told, during his two decades in power, Meles was able to outwit, outthink, outsmart, outplay, outfox and outmaneuver, and neutralize his opposition at will. Meles’ disciples today trumpet their determination to walk in his footsteps and do exactly the same thing.

Where is the "opposition" now?
 
Perhaps it is premature to pose the question, "Where do we go from here?" to Ethiopia’s "opposition". It may be more appropriate to ask where the "opposition" is (is not) now. From my vantage point, the "opposition" is in a state of resignation, stagnation, negation, frustration and alienation. I see the "opposition" watching with hypnotic fascination the abusers of power chasing after their tails. The "opposition" seems anchorless, agenda less, aimless, directionless, dreamless and feckless. The "opposition", it seems to me, is in a state of slumber, in crises and in a state of paralysis.


Time was when the "opposition" got together, stood together, put heads together, worked together, campaigned together, negotiated together, compromised together, met the enemy together and even went to jail together. Flashback 2005! The "opposition" set aside ethnic, religious, linguistic, ideological and other differences and came together to pursue a dream of freedom and democracy. That dream bound the opposition and strengthened the bonds of their brotherhood and sisterhood. The "opposition" mobilized together against factionalism and internal conflicts and closed ranks against those who sought to divide and split it. By doing so, the opposition thumped the ruling party in the polls.

 
In the past seven years, the dream of democracy and freedom among the "opposition" seems to have slowly faded away and the strength of its champions sapped away in mutual distrust and recrimination. Dialogue in the "opposition" has been replaced with monologue and deafening silence; action with inaction; cooperation with obstruction; coalition with partisanship; unity with division; amity with enmity and civility with intolerance.

 
The "opposition" wants change and rid Ethiopia of tyranny and dictatorship. But as Dr. Martin Luther King, Jr. said, "Change does not roll in on the wheels of inevitability, but comes through continuous struggle. And so we must straighten our backs and work for our freedom. A man can’t ride you unless your back is bent. … We know through painful experience that freedom is never voluntarily given by the oppressor; it must be demanded by the oppressed." The Ethiopian "opposition" needs to stand up erect and make demands with steely ackbone and stiff upper lip.

There are many ways to stand up and show some backbone. To speak up for human rights and against government wrongs is to stand up. To demand that wrongs be righted is to stand up. To open up one’s eyes and unplug one’s ears in the face of evil is standing up. To simply say "No!" even under one’s breath is standing up. Speaking truth to power is standing up. Dr. King said, "A just law is a manmade code that squares with the moral law or the law of God. An unjust law is a code that is out of harmony with the moral law." Standing up against an unjust law is standing up for justice.

In January 2011, I wrote a weekly column entitled, "
After the Fall of African Dictatorships" and posed three questions: "What happens to Africa after the mud walls of dictatorship come tumbling down and the palaces of illusion behind those walls vanish? Will Africa be like Humpty Dumpty (a proverbial egg) who "had a great fall" and could not be put back together by "all the king’s horses and all the king’s men"? What happens to the dictators?"

 
The mud walls of dictatorship in Ethiopia have been exhibiting ever expanding cracks since the death of the arch architect of dictatorship Meles Zenawi sometime last summer. The irony of history is that the question is no longer whether Ethiopia will be like Humpty Dumpty as the "king" and "king’s men" have toiled to make her for two decades. The tables are turned. Despite a wall of impregnable secrecy, the "king’s men and their horses" are in a state of disarray and dissolution. They lost their vision when they lost their visionary. The old saying goes, "in the land of the blind, the one-eyed man is king." Well, the king is no more; and the "king’s men and horses" are lost in the wilderness of their own wickedness, intrigue and deception.

The "fierce urgency of now" is upon Ethiopia’s opposition leaders to roll out their plans and visions of democracy. Now is the time for Ethiopia’s human rights advocates to bring forth their vision of a society governed by the rule of law. Now is the time for Ethiopia’s civil society leaders to build networks to connect individuals and communities across ethnic, religious, linguistic, gender and regional lines

 
Now is the time for Ethiopia’s intellectuals to put forth practical solutions to facilitate the transition from dictatorship to democracy. Now is the time for all freedom loving Ethiopians to come forward and declare and pledge their allegiance to a democracy, human rights and the rule of law. Now is the time to unchain ourselves from the burdens of the past. Now is the time to abandon the politics of identity and ethnicity and come together in unity for the sake of all of Ethiopia’s children. Now is the time to organize and mobilize for national unity. Now is the time for truth and reconciliation. Now is the time to assert our human dignity against tyrannical barbarity.

Now is not the time to for division, accusation and recrimination. Now is not the time for finger pointing, bellyaching and teeth gnashing. Now is not the time to remain silent. Now is not the time to turn a blind eye. Now is not the time to turn a deaf ear.

Where should we go from here? 
 

I will try to answer my own question in brief form for now. The opposition should get on the highway that leads to democratic governance. The opposition should roll out its action plan for a democratic, post-dictatorship Ethiopia. The principal lesson to be learned from the experiences of the past seven years is that the opposition’s role is not simply to "oppose, oppose and oppose" for the sake of opposing.

 
The opposition’s role and duty goes well beyond simply proclaiming opposition to the abusers of power. The opposition’s role goes to the heart of the future democratic evolution and governance of the country. In that role, the opposition must relentlessly demand accountability and transparency of those absuing power. The fact that the abusers of power will pretend to ignore demands of accountability and transparency is of no consequence.

 
The question is not if they will be held to account but when. The opposition should always question and challenge the actions and omissions of those abusing their powers in a principled and honest manner. The opposition must analyze, criticize, dice and slice the policies, ideas and programs of those in power and offer better, different and stronger alternatives. It is not sufficient for the opposition to publicize the failures and of the ruling party and make broad claims that they can do better.

For starters, the opposition should make crystal clear its position on accountability and transparency to the people. For instance, what concrete ideas does the opposition have about ending, or at least effectively controlling, endemic corruption in Ethiopia. 
In an exhaustive 448-page report, the World Bank recently concluded that the Ethiopian state is among the handful of the most corrupt in the world. I cannot say for sure how many opposition leaders or anyone in the opposition has taken the time to study this exquisitely detailed study of corruption in Ethiopia; but anyone who has read the report will have no illusions about the metastasizing terminal cancer of corruption in the Ethiopia body politics. The opposition should issue a white paper on what it would do to deal with the problem of corruption in Ethiopia.

Speaking truth to the powers that could be
 
I know that what I have written here will offend some and anger others. Still many could find it refreshing and provocatively audacious. Some critics will wag their tongues and froth at the mouth claiming that I am attacking the "opposition" sitting atop my usual high horse. They will claim that I am weakening and undermining the "opposition" preaching from my soapbox. Others will say I am overdramatizing the situation in the "opposition".

 Still others will claim I am not giving enough credit or am discrediting those in the "opposition" who have been in the trenches far longer than I have been involved in human rights advocacy. They will say I am doing to the opposition what the power abusers have done to them. They will say I don’t understand because I have been sitting comfortably in my academic armchair and have not been on the front lines suffering the slings and arrows of an outrageous dictatorship. Be that as it may!

 
Though I acknowledge such claims could be convenient diversions, there are two essetnial questions all of us who consider ourselves to be in the "opposition" can no longer ignore and must be held to answer: They are pedaling backwards on the low road of dictatorship, are we marching forward on the highway to democracy? Is the "opposition" better off today than it was in 2005?

Professor 
Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino and is a practicing defense lawyer.

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar