torsdag 31. oktober 2013

የአማራ ወጣቶች ንቅናቄ የተነሳለትን ዓላማ አስረዳ

(ዘ-ሐበሻ) የአማራ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ (አወጋን) በሚል ራሱን የሚጠራው ድርጅት ከሰሞኑ በኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ላይ እርምጃ እየወሰድኩ ነው የሙሉ መግለጫዎችን ሲያወጣ ነበር። ይህን ተከትሎ አወጋን ማን ነው? ዓላማውስ ምንድን ነው? የሚሉ የተለያዩ ጥያቄዎች ከአንባቢያን ይነሳሉ። አወጋን ይህን ጥያቄ ለመመለስ ዓላማውን እና ለምን መመሥረት እንዳስፈለገው በጽሑፍ ይተነትናል። መልካም ንባብ፦

መግቢያ 

የአማራ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ አማራው ወዶ ሳይሆን ተገዶ እራሱን ከፈፅሞ ጥፋት ይታደግ ዘንድ በአማራ ተወላጅ ወጣቶች ና ሙህራን የተመሰረተ የነፍሳድን ቡድን ሲሆን በአንዲህ አይነት አላማ የተደራጁ የፖለትካም ሆነ የሲቪል ማሃበራትን የሚደግፍ እና መታሰቢያነቱ ከመተከል አውራጃ አማራ በመሆናቸው ብቻ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የመኪና አደጋ በሚል ሰበብ ጅምላ ግድያ ለተፈፀመባቸው ንፁሃን አማራ ወገኖቻችን ነው ::
አወጋን ማለት ምን ማለት ነው ?
አወጋን የፖለቲካ ድርጅት ወይንም ነፃ አውጭ ግንባር አይደለም ነገር ግን ኢትዮጵያዊነቱን በመቀማት ላይ የለውን እና በተደጋጋሚ አራሱን እንደወንጀለኛ እንዲቆጥር የተደረገውን የተሳሳተ ፀረ-አማራ አስተምህሮ እና ስብከት ከአማራ ተወላጅ እንደበት እንዲሁም ይህን ፀረ-አማራ ስብከት ለተሰበኩ እና ለአማራ ህዝብ መጥፎ አመለካከት እንዲያድርባቸው በተደረጉ ኢትዮጵያውያን ዘንድ አስወግዶ እውነቱን ና የኢትዮጵያ ታሪክ የሚያስተምረውን በማሳወቅ ና በማስተባበር የአማራ ወጣት ቀጣዩን የሀገርን እድል እጣ ፋንታ መወሰን ሚያስችለውን ስነልቦናዊ እና አካላዊ ብቃት ለመፍጠር የሚደረግ የወጣቶች እንቅስቃሴ ነው ፡፡
አወጋን በዋናነት የሚታገለው ፡-
ከአንድ የፖለቲካ ድርጅት ፤ ከአንድ የፖለቲካ ድርጅት መሪ ፤ ከገዥው ፓርቲ የቋንቋ ትስስር ካላቸው ጎሳወች ወይም ብሔሮች ጋር ሳይሆን አማራን በዳይ አስመስሎ ከሚነዛ ፀረ-አማራ የፖለቲካ አስተሳሰብ ጋር ነው ;
አወጋን አማራው በኢትዮጵያዊነቱ ሀገር ወዳድ በመሆኑ እና ለአንድነት መሰረት ሁኖ መታየቱን እንደ ወንጀል የሚቆጥሩት እና የኢትዮጵያን ና የኢትዮጵያውያንን በመከባበር ላይ የተመሰረተ የጋራ አንድነትን አጥብቀው በሚጠሉ ባዕዳን እና ባለፉት የውጭ ሀገር የወረራ ሰዓት አባቶቻቸው ስህተት ሰርተው በታሪክ ተወቃሽ ያደረጓቸው የከዳተኛ ልጆች ራሳቸውን ከታሪክ ተወቃሽነት ለማዳን በአማራው ላይ የጥላቻ የፀረ-አማራ ፖለቲካ ስብከት የተፈፀመውን እና የሚፈፀመውን ወንጀል በመመከት አማራው አሁንም ሳያወላውል እና አንዳቺም ወደኋላ ሳይል ኢትዮጵያን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን አባቶች፤ እናቶች፤ወንድምች እና አህቶቹ ጋር በመሆን ጠብቆ እንዲኖር የሚያነሳሳ የመጀመሪያ ዙር ትግል ነው ::
አማራው ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ማለቱን እንደወንጀል የሚቆጥሩት በኢትዮጵያዊነት ዉስጥ ምንም የታሪክ ድርሻ የሌላቸው የባንዳ ልጆች አማራውን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እየገደሉት፤ አያስገደሉት ምዕተ አመትን ያስቆጠሩ ሲሆን ከዚህ ማሃበረሰብ አብራክ የወጡ ልጆች ሳይቀሩ ነጣጥሎ ማየት እና የዚህ ህዝብ ችግር መፍትሄ በመስጠት ፋንታ ደጋግመው ስለነገሯቸው ውሸት ግራ ተጋብተው አንዳንዶቹም ስለ ወገናቸው አንስተው ቢናገሩ ዘረኛ አንባላለን በሚል ደካማ አስተሳሰብ እና አንዳንዶቹ የሚያገኙት ጥቂት የስልጣን ወይንም የስጦታ መጠን ይቀንስብናል ብለው በሚያስቡ ሆዳሞች ችል ተብሎ አማራው በእጅጉ ተጎድቷል እየተጎዳም ይገኛል፡፡ፀረ-አማራ ጽንሰ ሀሳብ (manifesto) ይዘው በተነሱ አናሳና ደካማ ግለሰቦች በመሰረቷቸው ድርጅቶች ወያኔና ሻብያ በአማራ ላይና በኢትዮጵያ ላይ ያደረሱተንና እያደረሱ ያሉትን ስህተት፤ወንጀል ና ግፍ ለአማራና ለኢትዮጵያ ህዝብ መዘርዘርና በመዘርዘር ለማሳወቅ መሞከር “ልጅ ለናቷ ምጥ አስተማረች” እንዳይሆን የችግሩ ገፈት ቀማሽ በመሆናቸው ዱዳዩ ተዘርዝሮም ስለማያልቅ እንዴው ለወጉ ያክል፤
አማራ የሆነ ምርኮኛ በሙሉ ይገደል ነበር ፤ አማራ ህሙማን በሆስፒታል እንደተኙ በሙሉ በጥይት ተፈጅተዋል ፤ አማራው ከገዥው ፓርቲም ሆነ ተቃዋሚ ነኝ ብለው ከሚታገሉ ድርጅቶች ሞት ብቻ ተችሮት በቀይ ሽህብር እና ነጭ ሽብር በተሰኘው ቀውስ አማራው ቀዳሚ ተጠቂ ነበር ፤ ወያኔ እና ሻቢያ ትግላቸው በዋናነት ፀረ-አማራ ነበር ፤አማራው ከዚህ ሁሉ አምልጦ ከሀገር እንዳይወጣ በጎረቤት ሀገሮች ጽ/ቤት ከፍተው እና ተደራጅተው አማራ የሆነውን በሙሉ ያስገድሉት ነበር ( በ ሶማሊያ፤ በጅቡት፤ በሱዳን ፤ በኬንያ ) አማራ የሆነ እና ጉራጌ ወንድሞቻችን እየተመረጡ በሌላ አስር ቤት እየታጎሩ እና ያለ ፍርድ ትዕዛዝ ደካማ አመለካከት ባላቸው ጎሳዎች አማራ በመሆናቸው ብቻ እንደ ወንጀል ተቆጥሮ አንገታቸው አንደበግ ይታረዱ ነበር ::
አወጋን ይሄን በዘረኝነነት ላይ የተመሰረተን ፀረ-አማራ እና ታሪክ አልባ የሆኑ ጥቂት ደካማ የባናዳ ልጆች የፈጠሩትን የተሳሳተ አስተሳሰብ ላይ የተመሰረተ የጥላቻ ድርጅት ዳግም አንዳይነሳ አፈራርሶ መቅበርና በቦታው በመዋደድ እና መከባበር ላይ ፅኑ የአንድነት ስርዓት እንዲመሰረት እና አማራ በዳይ አለመሆኑን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን በማስገንዘብ ብሔራዊ አርቅ ተደርጎ መካሰስ እና መበቀቃል አንዲቀር በጋራ ለሚመሰረተው ጠንካራ ስርዓት አማራው እራሱን ብቁ እንዲያደርግ የሚያደርግ የመጀመሪያ ዙር ትግል ነው :http://www.zehabesha.com/amharic/archives/8753:
ድል ለወጣቶች የህዝብ ልጆች
ሞት ለዘረኞች የሕዝበ ጠላቶች

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar