tirsdag 30. juli 2013

ፖለቲካ ስለበቃን ወደ ሕዝቡ ሄደን ማስተማርና መቀስቀስ አለብን›› አቶ አስራት ጣሴ፣ የአንድነት ፓርቲ ዋና ጸሐፊ

‹የቢሮ Posted: 28 Jul 2013 02:04 PM PDT
28 July 2013 

ሰሞኑን በኢትዮጵያ ተቃውሞ ፖለቲካ ጎራ ብዙም ባልተለመደ ሁኔታ የምርጫ ወቅት ከመድረሱ ‹‹እጅግ›› ቀደም ብሎ ሕዝባዊ ስብሰባና ሠልፍ እዚህም እዚያም እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በቀጣይነትም በተለያዩ ፖለቲካዊ አጀንዳዎች ጥላ ሥር በርካታ ሠልፎችንና ሕዝባዊ ስብሰባዎችን ለመጥራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ታውቋል፡፡

ባለፉት ሳምንታት ሕዝባዊ ሠልፎችንና ስብሰባዎችን ካካሄዱ ተቃዋሚ ድርጅቶች መካከል በቅርቡ የተመሠረተው ሰማያዊ ፓርቲ፣ በተቃውሞ ፖለቲካ ውስጥ የጎላ ተሳትፎ ያለው አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ (አንድነት) ፓርቲና የስድስት ፓርቲዎች ግንባር የሆነው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ናቸው፡፡ እነዚህ የፖለቲካ ድርጅቶች በአዲስ አበባ፣ በመቀሌ፣ በጎንደርና በደሴ ከተሞች ሕዝባዊ ሠልፎችንና የተቃውሞ ስብሰባዎች አካሂደዋል፡፡ እነዚህ ድርጅቶች በቀጣይነትም በተለያዩ ቦታዎች የተቃውሞ አንቅስቃሴዎችን ለማካሄድ እየተዘጋጁ መሆኑ ታውቋል፡፡ ይህንን ወቅታዊ ጉዳይ በተመለከተ የመድረክ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የአንድነት ፓርቲ ዋና ጸሐፊ አቶ አስራት ጣሴን ውድነህ ዘነበ አነጋግሯቸዋል፡፡ አቶ አስራት በኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ ዙርያ የነቃ ተሳትፎ ከሚያደርጉ ግለሰቦች መካከል ተጠቃሽ ናቸው፡፡

ሪፖርተር፡- ሰሞኑን የእርስዎ ፓርቲ በጎንደርና በደሴ የተቃውሞ ትዕይንተ ሕዝብ አካሂዷል፡፡ ፓርቲው ለሕዝቡ ምን ማሳየትና ምን ማድረግ ፈልጐ ነው ትዕይንቱን ያካሄደው?

አቶ አስራት፡- ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት ትንሽ ወደኋላ መለስ ማለት ያስፈልጋል፡፡ ከ2002 ምርጫ በኋላ አንድነትም እንደ አንድነት፣ ሌሎቹም ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ቢሆኑ ሕዝብ ውስጥ ገብተው የማንቃት ሥራና ሕዝባዊ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሥራ በተገቢው አልሠሩም፡፡ በጭራሽ በተገቢው መንገድ አልተሠራም፡፡ እርግጥ ሁልጊዜ ማማኸኛ አለን፡፡ ጥርጥር የለውም አዳራሽ ማግኘት አይቻልም፡፡ ሰላማዊ ሠልፍ መውጣትም አይቻልም፡፡ ብዙ ጊዜ አዳራሽ እየተከራየን ገንዘባችሁን መልሳችሁ ውሰዱ እየተባልን ተቸግረን ነበር፡፡ በሌላ በኩልም ስናየው ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ለአንድነት ፓርቲ ትልቁ መሣርያ ነበር፡፡ ሕዝብን ለማደራጀትና ለማንቃት፤ እንደገና ከሕዝቡም የሚመጡ ሐሳቦችን የምናገኝበት ነበር፡፡ በተለያዩ ስልቶች ጋዜጣው ከሕትመት እንዲወጣ ተደረገ፡፡ መጀመርያ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት እንዳያትም ተደረገ፡፡ ጋዜጣው እንዳይታተም ለተደረገበት የሚሰጡ ምክንያቶች ሁሉ በቀልድና ሹፈት ደረጃ የሚታዩ ናቸው፡፡ 

በግል ማተሚያ ቤቶችም አንድ ጊዜ ያትሙልንና በድጋሚ ልናሳትም ስንሄድ ‹‹እባካችሁ ልጆቻችንን እናሳድግ›› ይሉናል፡፡ ቀብድ ወስደውም የማያትሙና ገንዘቡን አሻፈረኝ ብለው የሚመልሱ አሉ፡፡

ይህንን ያነሳሁት ሕዝብን ለማንቀሳቀስ ዕድሎቹ በጣም ጠበቡ ለማለት ነው፡፡ ይህ ውጫዊ ችግራችን ነው፡፡ ነገር ግን ወደዚህ እንቅስቃሴ ከመግባታችን በፊት አንዳንዶቻችን ራሳችን ማፈር ጀምረን ነበር፡፡ እኔ በግሌ ማፈር ከጀመርኩ ቆይቻለሁ፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ ሆኖ የፖለቲካ ሥራ መሥራት ወይም መምራት ካልተቻለ አስቸጋሪ ነው፡፡ አንዳንዶቻችን ኢንተርቪው ሰጪዎች ብቻ ሆንን፡፡ ኢንተርቪው ሰጪ የቢሮ ፖለቲከኞች ከሆንን ይህ አካሄድ የፖለቲካ ሥራን አይመጥንም፡፡ ፖለቲካን በቢሮ ውስጥ ሆኖ መሥራት አመራሮቻችንን አይመጥንም፡፡ አጥራችንን ሰብረን መውጣት አለብን፡፡ ሕዝቡ መሀል ገብተን ሕዝባዊ እንቅስቃሴ መፍጠር አለብን፡፡ ያለበለዚያ በአንዳንዶቻችን እምነት በእውነት አስፈላጊዎች አይደለንም፡፡ ምናልባት ረዥም ጊዜ ፖለቲካው ቦታ ላይ ኃላፊነት ይዘን በመቆየታችን፣ በወጣቶች ሊሠራ የሚችለውን ሥራ የዘነጋን ይመስለናል፡፡ ራሳችንን መታዘብ ደረጃ ላይ በመድረሳችን የሆነ ነገር መደረግ አለበት አልን፡፡ አጥራችን መሰበር አለበት፡፡ ሕገ መንግሥታዊ መብታችንን ማስከበር አለብን፡፡ ይህንን መሠረት አድርገን ወደ ሕዝብ እንሂድ ብለን ነው የተነሳነው፡፡

ሪፖርተር፡- ሰላማዊ ሠልፎችን ከዚህ ቀደም ማካሄድ የተዘጋ ነው ብለውኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት በጎንደርና በደሴ ማካሄድ ችላችኋል፡፡ አሁን መንግሥት ተለሳልሶ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ማለት ይቻላል?

አቶ አስራት፡- እኔ ከኢሕአዴግ በኩል ምንም የመለሳለስ ሁኔታ አላየሁም፡፡ የመለሳለስ ሁኔታ አላየሁም ስል በሁለቱም ቦታዎች ያካሄድናቸውንና በአዲስ አበባ ለማካሄድ ያሰብነውን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ደሴ ላይ በጭራሽ ልናደርግ እንዳንችል ተገቢ ባልሆነ መንገድ እንቅፋት ሲፈጥሩ ነበር፡፡ በተለይ በጎንደር እኔ በነበርኩበት ቦታ እገታ ጭምር ነበር፡፡ የእኛ የሥራ አስፈጻሚ አባላት፣ የብሔራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢው፣ የብሔራዊ ምክር ቤት አባሎቻችንና መኪኖቻቸው ሳይቀሩ እንዳይንቀሳቀሱ ተደርገው ነበር፡፡ የከተማው ከንቲባና የዞኑ መስተዳድር አናነጋግራችሁም፣ እንዲያውም አልፎ ተርፎ በዚህ ከተማ ምንም ዓይነት ሰላማዊ ሠልፍ አይሞከርም ብለው ነበር፡፡

ምክንያታቸውም አካባቢው የፀጥታ ችግር ያለበት ስለሆነ እዚህ የመጣችሁት ግርግር ለመፍጠር ነው የሚል ነው፡፡ በአደባባይ ሰው በሚሰማበት ቦታ ላይ ‹‹እደፋሃለሁ፣ እንደፋችኋለን፤›› እየተባልን ነበር፡፡ እስከ መጨረሻው ድረስ ያነጋገረን ኃይል አልነበረም፡፡ የትኛውም መስዋዕትነት ይከፈል፣ የሚያስከፍለውን ያህል ዋጋ ያስከፍል እንጂ ሰላማዊ ሠልፉን እንወጣለን አልን፡፡ በሕጉ መሠረት መከልከል አይችሉም፡፡ የሚፈለገው ማሳወቅ ነው፡፡ ሠልፍ እንደምናካሂድ አሳውቀናል፡፡ በዚህ መሠረት ተዘጋጅተን ስንጠብቅ ከፖሊስ ውይይት እናድርግ የሚል ጥሪ ቀረበልን፡፡ ከተወያየን በኋላም ብዙ ተፅዕኖ ተደርጎብንም ቢሆን ሠልፉን አድርገናል፡፡     
  
ሪፖርተር፡- ሠልፎቹን ከማካሄዳችሁ በፊት ግምት ይኖራችኋል ብዬ አስባለሁ፡፡ እናንተ ያሰባችሁትን ያህል ሠልፈኛ መጥቶላችኋል? ይህንን የምጠይቅዎ በተፅዕኖም ሆነ በሌላ ምክንያት የወጣው ሕዝብ ቁጥር አነስተኛ ነው የሚሉ ስላሉ ነው፡፡

አቶ አስራት፡- እኛ ቁጥርን በሁለተኛ ደረጃ ነው የምናየው፡፡ አንደኛው መርህ ነው፡፡ የቢሮ ፖለቲካ በቃ፡፡ የቢሮ ፖለቲካ ስለበቃን ወደ ሕዝብ ሄደን ማስተማርና መቀስቀስ አለብን፡፡ ሕዝቡ ለሕገ መንግሥታዊ መብቱ እንዲቆም መቀስቀስ አለብን፡፡ ከገባበት የፍርኃት ቆፈን እንዲወጣ ወደ ሕዝቡ ሄደን ሊከፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ከፍለን መሥራት አለብን የሚለው አንዱ ትልቁ ስኬት ወይም ግኝት ነው፡፡ ከስምንት ዓመት በኋላ ነው በጎንደር ሰላማዊ ሠልፍ የተካሄደው፡፡ በሁለተኛ ደረጃ እንዳልከው ብዙ ሕዝብ መጠበቅ አንድ ሰላማዊ ሠልፍ የሚጠራ ክፍል ተግባር ነው፡፡ ብዙ ሕዝብ ባገኘ ቁጥር የፖለቲካ ትርጉሙ ትልቅ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ በአሁኑ ጊዜ ለመጀመርያ ጊዜ በሚካሄዱ ሰላማዊ ሠልፎች በእውነት የናረ ቁጥር አዕምሮአችን ውስጥ የለም፡፡ መቼስ የወጣውን ሰው አትቆጥርም፡፡

መንግሥትም ታች አውርዶ ይገምታል፡፡ እኛም ትንሽ ከፍ እናደርግ ይሁን አናውቅም በጎንደር ከ20 እስከ 25 ሺሕ ሰው ወጥቷል፡፡ በደሴ ደግሞ እስከ 50 ሺሕ ሰው ወጥቷል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ለእኔ ቁጥር ሁለተኛ ደረጃ ነው፤ ወደፊት ግን ቁጥርም አስፈላጊ ነው፡፡ ሕዝቡ በገፍ ወጥቶ ያለውን ችግር በመግለጽ ያለውንም ድጋፍ ለተቃዋሚዎች ካላሳየ አስቸጋሪ ነው፡፡ ችግር አለ ማለት ነው፡፡ እኛ ውጤታማ ነበርን ነው የምንለው፡፡
 
ሪፖርተር፡- በሕጉ መሠረት ሰላማዊ ሠልፍ ለማካሄድ ማሳወቅ እንጂ ማስፈቀድ አይጠበቅም፡፡ ቀደም ሲል ሰላማዊ ሠልፍ ለማካሄድ ተከለከልን ትሉ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት ሰላማዊ ሠልፍ እያካሄዳችሁ ነው፡፡ ምን የተለየ አሠራር መጣ?

አቶ አስራት፡- ጥያቄው ትንሽ ከበድ ይላል፡፡ ከበድ ይላል የምልበት ከምን አንፃር ነው? ቅድም ካነሳሁት አንፃር በእውነት ቀደም ሲልም አሳውቀን መውጣት ነበረብን፡፡ እኛ ዝም ብለን ይህ ነው በማንለው ምክንያት [አልወጣንም]፡፡ አንዱ ፍርኃት መሆን አለበት፡፡ መቼም በ1997 ዓ.ም. የደረሰውን የሕዝብ እልቂት አይተናል፡፡ የሥርዓቱን የመጨረሻ የአምባገነንነት ደረጃም ተመልክተነዋል፡፡ ለሃያ ሁለት ወራት እስር ቤት በነበርንበት ጊዜ ያለምንም ምክንያትና ማስረጃ በዘር ማጥፋት መክሰስ የሚችል ሥርዓት መሆኑን ተረድተናል፡፡ እንደምታውቀው ከጥቅምት 1998 ዓ.ም. ጀምሮ 100 ሺዎች ለእስር ተዳርገው ነበር፡፡ በክፉ ቦታዎች ነበር እስሩ፡፡ በሰውነታቸው ላይ የደረሰ ጉዳት ነበር፡፡

ቅንጅትን ደግፎ የተነሳው ክፍልም ተመቷል፡፡ እኛም በእነዚህ ምክንያቶች ረጋ ብለን እንድናስብ ሆነናል፡፡ ያ ጊዜ ተመልሶ ይመጣል የሚል ሥጋት በመኖሩ ረዘም ላለ ጊዜ ማለትም ለአራት ዓመት የአየሩንና የሕዝቡን ሁኔታ ስንለካ ነበር፡፡ አንድ ወቅት ግን መቆም አለበት፡፡ ወይ ፖለቲካውን ፖለቲካ አድርገን እንሥራው ወይ እንተወው፡፡ ካልሠራነው ለሚሠሩ ሰዎች እንተው በሚለው ጉዳይ ደጋግመን ተነጋገርንበት፡፡ ከዚያም ሕገ መንግሥቱንና መብታችንን እናስከብራለን፡፡ መብታችንን ለማስከበር በምናደርገው እንቅስቃሴ የሚደርስብንን ሁሉ እንቀበላለን በሚል ነው ይህ እንቅስቃሴ የተጀመረው፡፡
  
ሪፖርተር፡- ብዙ ጊዜ ተቃዋሚዎች ሰላማዊ ሠልፍና ቅስቀሳዎችን የምታካሂዱት ምርጫ በሚደርስበት ወቅት ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ አንድነትና ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች ምርጫ ከመድረሱ በጣም ቀደም ብላችሁ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናችሁ፡፡ ይህንን ልታደርጉ የቻላችሁበት የፖለቲካ ትንታኔ ምንድነው? በፖለቲካ ፓርቲዎች አካባቢ የአካሄድ ለውጥ ሊታይ የቻለበት ምክንያትስ ምንድነው?

አቶ አስራት፡- ያለንበት ሁኔታ ነው፡፡ አገራችን አደገኛ ወቅት ላይ ነው ያለችው፡፡ ጥናቶችን ልጥቀስ፡፡ ‹‹ዘ ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንት ዩኒት›› የዲሞክራሲ ደረጃን ለመለየት 60 መመዘኛዎችን ተጠቅሞ አገሮችን በአራት ከፍሏል፡፡ በዚህ መሠረት ሙሉ ዲሞክራሲ፣ እንከን ያለበት ዲሞክራሲ፣ ድቅል አገዛዝ (አንዳንዴ ዲሞክራሲ አንዳንዴ አምባገነን) እና የመጨረሻው የለየላቸው አምባገነን በሚሉ ክፍሎች ከፍሏል፡፡ በዚህ መመዘኛ ኢትዮጵያ የተመደበችው ፍፁም አምባገነኖች ከሚባሉት ውስጥ ነው፡፡

ሌላ ጥናት አለ፡፡ ‹‹ፍሪደም ሐውስ›› የሚባል ተቋም የነፃነት ደረጃን በሚመለከት አጥንቷል፡፡ ይህ ጥናት አገሮችን በሦስት ከፍሏል፡፡ ነፃ፣ ከፊል ነፃ፣ ነፃ ያልሆኑ በሚል ከፍሏል፡፡ አሁንም ኢትዮጵያ ነፃ ያልሆኑ በሚሉት ጎራ ውስጥ ነው የተመደበችው፡፡ መመዘኛዎቹ ግልጽ፣ ተዓማኒና ነፃ ምርጫ መካሄዱ፣ ውድድር ያለበት የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት መኖሩ፣ ፖለቲካዊ ፉክክር ያለበት ምርጫ መካሄዱ፣ የምርጫ ሚስጥራዊነት የተጠበቀ መሆኑና የነቃ የሕዝብ ተሳትፎ ያለበት መሆኑ እንደ መስፈርት ተቀምጧል ይላል፡፡ በዚህም ብትመለከት ኢትዮጵያ የተመደበችው ፍፁም ነፃ ያልሆኑ አገሮች ምድብ ውስጥ ነው፡፡

ከዚህ ሁሉ የሚያሰጋው ‹‹ፎሬን ፖሊሲ ሜጋዚንና ፈንድ ፎር ፒስ›› የሚባል ድርጅት ባደረገው ጥናት የዓለም አገሮች የሚገኙበትን የመረጋጋት ሁኔታ በተወሰኑ መስፈርቶች አወዳድሮ፣ ኢትዮጵያ ዝቅተኛ ነጥብ በማግኘት የመከነ አገር (ፌልድ ስቴት) ለመሆን ከተቃረቡትና አሳሳቢ ከተባሉት አገሮች ቀጥላ አደጋ ዞን ውስጥ ተመድባለች፡፡

እነዚህን ነጥቦች ያነሳሁት ጉዳዩ የሥልጣን ጉዳይ ስለሆነ ብቻ አይደለም፡፡ ጉዳዩ የአገር ህልውናም ጭምር ነው፡፡ ባለንበት ሁኔታ የሙስናውን ሁኔታ ታዩታላችሁ፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2000 እስከ 2013 ድረስ 16.5 ቢሊዮን ዶላር ከኢትዮጵያ ወጥቷል፡፡ ገንዘቡ የወጣው በሙስናና በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር አማካይነት ነው፡፡ በህዳሴ ግድብ ዋጋ ተመን ብንመለከተው ሦስት የህዳሴ ግድቦችን ይገነባል፡፡ ሕዝቡ በገፍ ይሰደዳል የኑሮ ውድነቱ ከፍቷል፡፡ ይኼ ጉዳይ አቅጣጫውን ስቶ ከመሄዱ በፊት የምንችለውን ያህል አገር የማዳን ሥራ መሠራት አለበት በማለት ነው የተነሳነው፡፡ እንደ አገርና እንደ ሕዝብ ለመቀጠል ጥያቄ ውስጥ ነው ያለነው፡፡  

ሪፖርተር፡-  የፖለቲካ ድርጅቶች ሁሉ እንቅስቃሴ የጀመራችሁት ይህንን አስባችሁ ነው? ከምርጫ በፊት እንቅስቃሴ ውስጥ የገባችሁት በዚህ መነሻነት ነው ማለት ይቻላል?

አቶ አስራት፡- የአንድነትን በድፍረት መናገር እችላለሁ፡፡ ሌሎችም ቢሆኑ ከዚህ የተለየ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ የአገሪቷን ተጨባጭ ሁኔታ፣ የሰፈነውን አምባገነናዊነት፣ የሰፈነውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ የፍርድ ቤቶችን ነፃ ያለመሆንና የሕግ የበላይነት የመሳሰሉት ችግሮች መከበር አለባቸው በሚል ነው፡፡ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ ሕገ መንግሥቱን ስድስትና ሰባት ቦታ ይጥሳል፡፡ በዚህ ምክንያት ነው የተነሳነው፡፡  

ሪፖርተር፡- ሕዝቡ እነዚህን ጉዳዮች እንዲረዳላችሁ ፈለጋችሁ እንበል፡፡ ከዚያ የሚቀጥለው መንግሥት እነዚህን ነጥቦች እንዲያስተካክል ነው? ወይስ በሥልጣን ጥያቄ ትገፋላችሁ?

አቶ አስራት፡- ግልጽ ነው፡፡ አንደኛ የፀረ ሽብር አዋጅ እንዲሰረዝ ነው የምንጠይቀው፡፡ ሁለተኛ የሕዝቡ ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ይከበሩ፡፡ መብትህን አስከብር ነው የምንለው፡፡ ሕዝቡ ነፃ ዳኝነት ያግኝ የሕግ የበላይነት ይከበር፡፡ መልካም አስተዳደር ከነጭራሹ የለም፡፡ መልካም አስተዳዳር መስፈን አለበት፡፡ ሙስና የሥርዓቱ መገለጫ ሆኗል፤ መቆም አለበት፡፡ ጥፋተኞች መቀጣት አለባቸው፡፡ መንግሥት በሕዝቡ ውስጥ ተገቢውን መረጋጋትና መግባባት ለመፍጠር አልቻለም፡፡ መንግሥት የሕዝብ አመኔታ ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ይህ ሊሆን ይችል ዘንድ ከጉዳዩ ባለቤት፣ ይመለከተናል ከሚሉ ባለድርሻዎች፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሲቪክ ማኅበራት፣ ከአገር ሽማግሌዎችና ከምሁራን ጋር ቁጭ ብሎ ብሔራዊ መግባቢያና ብሔራዊ የውይይት መድረክ መክፈት አለበት፡፡ ምክንያቱም አሁን ባለው ሁኔታ መንግሥት ሕዝቡንና አገሪቱን እያስተዳደረ አይደለም፡፡ መነጋገርና መወያየት አለበት፡፡

በምንም መንገድ ግን ተቃዋሚ ፓርቲ አንድነትም ሆነ እኔ በቅርብ የማውቀው መድረክም ከመንግሥት በአቋራጭ የሚጠይቁት የሥልጣን ጉዳይ የለም፡፡ ሥልጣን የሚመነጨው ከምርጫ ሳጥን ነው ብለን ነው የምናምነው፡፡ በዚህ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ አንዱ ሕዝብ ለመብቱ እንዲቆምና በ2007 ምርጫ ተገቢ ነው ብሎ የሚያስበውን ፓርቲ መርጦ ወደ ሥልጣን እንዲያመጣ፣ ኢትዮጵያ እንደ አገር አቅጣጫዋን እንድትይዝ ነው፡፡   

ሪፖርተር፡- የእርስዎ ፓርቲም ሆነ የታቀፈበት መድረክ በተካሄዱ ምርጫዎች ብዙም ተሳታፊ አይደሉም፡፡ በ2007 ዓ.ም. በሚካሄደው ምርጫ አቋማችሁን አሁን ላይ መናገር ከባድ ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን በምርጫ ንቁ ተሳታፊ ሳትሆኑ እነዚህ ቅስቀሳዎችን እንዴት ልትጠቀሙባቸው አስባችኋል? ከዚህ ጋር ደግሞ ሁለት ጊዜ ያልተወዳደረ ፓርቲ ከጨዋታ ውጭ ይሆናል የሚል የምርጫ ቦርድ ሕግ አለ፡፡

አቶ አስራት፡- ከምርጫ መሰረዝ ከሚለው ልነሳ፡፡ ይኼ የራሴ የግል እምነቴ ነው፡፡ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ነፃ፣ ፍትሐዊና ሚስጥራዊነቱ ባልተጠበቀ ምርጫ ከመሳተፍ ሁለት ጊዜ ሳይወዳደር ቢቀር የተሻለ ነው፡፡ ምክንያቱም ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ያሰፍናል፣ የሕግ የበላይነትን ያመጣል፡፡ የምንለው ትልቁ መሣሪያ ካልተስተካከለና ፍትሐዊና ግልጽ ካልሆነ በስተቀር በአገራችን እየተዳደርን ያለነው በ2002 ዓ.ም. በተካሄደው የውሸት ምርጫ ነው፡፡ በውሸት ምርጫ መሳተፍ የሕዝብን ብሶትና መከራ ለማራዘም መተባበር ነው፡፡ ስለዚህ ያ ሊያሳስበን አይገባም፡፡

በአዲስ አበባ የአካባቢ ምርጫ ያልተሳተፍንባቸው ምክንያቶች ግልጽ ናቸው፡፡ 18 ጥያቄዎችን ለምርጫ ቦርድና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅርበናል፡፡ ሊያወያዩንና ሊያነጋግሩን አልፈለጉም፡፡ 99.6 በመቶ [አሸንፈናል] ያሉትን ልንደግመው አንፈልግም፡፡  

ሪፖርተር፡- በርካታ አገሮች የፀረ ሽብር ሕጎች አሏቸው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥትም እንደሌሎች አገሮች የፀረ ሽብር ሕግ አውጥቷል፡፡ አንድነት የፀረ ሽብር ሕጉ ይሰረዝ ሲል አማራጭ አቅርቦ ነው? ሌላ ዓይነት አማራጭ ይጠቀማል? ወይስ ከነጭራሹ አያስፈልግም ነው የሚለው?

አቶ አስራት፡- በመሠረቱ በምናውቀው የኢትዮጵያ ታሪክና ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ኢትዮጵያ ለሽብር ተጋላጭ አይደለችም፡፡ በአገራችን ሽብር የሚፈጥሩ አሉ ብለን አናምንም፡፡ ሽብር ቀልድ አይደለም፡፡ ሽብርን የምናውቀው በአፍጋኒስታን ታሊባን የሚያካሂደውን ሽብር ነው፡፡ የነአልቃይዳ ትልቅ ሽብር ነው፡፡ የሶማሊያ አልሸባብ ትልቅ ሽብር ነው፡፡ የናይጀሪያው ቦኮሐራም ትልቅ ሽብር ነው፡፡ ኢትዮጵያ ለእንደዚህ ዓይነት ሽብር የተጋለጠች አገር አይደለችም፡፡ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጧ አሳሳቢ ቢሆንም፣ በተጨባጭ ግን ይህ የሽብር አዋጅ በወጣበት ጊዜ ኢትዮጵያ እንደዚህ ዓይነት የሽብር ሥጋት አልነበረባትም፡፡

ይህ የፀረ ሽብር አዋጅ የወጣው ኢትዮጵያ ለሽብር ተጋልጣ ሳይሆን ተቃዋሚ ፓርቲዎችን፣ በነፃ ፕሬስ ላይ የተሰማሩትንና በሲቪክ ማኅበራት የተሰማሩትን ለማፈን ነው፡፡ በእኛ በኩል ኢትዮጵያን ለሽብር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ተመጣጣኝ የሆነ ሕግ፣ ተመጣጣኝ የሆነ አዋጅ እንዲኖር እናደርጋለን፡፡ ነገር ግን መኪና በሌለበት አገር የትራፊክ ሕግ ለማውጣት የመሞከር ዓይነት ነው መንግሥት እያደረገ ያለው፡፡ በዚህ ፀረ ሽብር ሕግ ሌላው መታየት ያለበት ኢትዮጵያ ውስጥ ለጥፋት ወይም ለወንጀል የሚሰማሩ ካሉ የኢትዮጵያ ሕግ ይዳኛቸዋል፡፡ ይህ እኮ በቀጥታ መብትን መንፈግ ነው፡፡ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ እኮ ነው ሕጉ ሊያስር፣ ቤት ሊበረብርና ደም መውሰድ የሚችለው፡፡ 

ሪፖርተር፡- ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎችና ጊዜያት የቦምብ ፍንዳታዎች ተከስተው የሰው ሕይወት እንደጠፋ ይታወቃል፡፡ አደጋ ከመድረሱ በፊትም ከነጦር መሣርያዎቻቸው የተያዙ አሉ፡፡ የፀረ ሽብር ሕጉ እንዲወጣ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል እነዚህ ተጠቃሽ መሆናቸውን መንግሥት ገልጿል፡፡ እነዚህን በተመለከተ የእናንተ ሐሳብ ምንድነው?

አቶ አስራት፡- እንደ ግለሰብ በእነዚህ ክስተቶች የአሸባሪነት ባህሪ እየመጣ ነው የሚል ሥጋት ለመፍጠር ተፈልጎ እንጂ፣ ለአንዱም ጉዳይ በትክክል የምናገኘው መረጃ የለም፡፡ እስከ መጨረሻ ወጥቶ ለምሳሌ ለፕሬስ በትክክል እነዚህ ሰዎች ማናቸው? ምን አደረጉ? የሚባለው ነገር ተመርምሮ አልቀረበም፡፡ ሕዝብ እኮ መረጃው ቀርቦለት እውነትም አላለም፡፡ እንዲሁ ትንሽ ችግር በመፍጠር ወቅቱን እየተከተሉ ተቃዋሚዎችን ወይም ሊያጠቁ የሚፈልጉትን ክፍል ለማጥቂያ የሚደረግ አካሄድ ነው ብዬ ነው የማየው፡፡ በአገርና በሕዝብ ላይ ትልቅ ሥጋት መጥቶ ነበር የሚል እምነት የለኝም፡፡

ሪፖርተር፡- አንድነትና ዓረና የመድረክ አባል ድርጅቶች እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ አንድነትና ዓረና ከመድረክ ውጭ ራሳቸውን ችለው ቅስቀሳ ማካሄዳቸው ታይቷል፡፡ በተለይ አንድነት ከመድረክ ጋር በቅርቡ በጀመረው እሰጥ እገባ ይሆን ለብቻው ቅስቀሳውን ያካሄደው?

አቶ አስራት፡- አንድ መረጃ ላስተካክልልህ፡፡ መቀሌ የተካሄደው ሕዝባዊ ስብሰባ በመድረክ አማካይነት ነው፡፡ እኛም [አንድነት] ትግራይ ቤዝ አለን፡፡ ዓረናም ትግራይ ቤዝ አለው፡፡ በአብዛኛው በዚያ አካባቢ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርገው ዓረና በመሆኑ የዓረና መስሎ ነው እንጂ ስብሰባው በመድረክ ስም የተካሄደ ነው፡፡

ሌላው እውነት ነው በመድረክና በአንድነት መካከል የተወሰኑ አለመግባባቶች ተፈጥረዋል፡፡ ለእነዚያ አለመግባባቶች መንስዔ የነበረው አንድነት ስትራቴጂካዊ ፕላኑ በሚመራው አቅጣጫ መሠረት ከመድረክ ጋር ያለውን ግንኙነት እንዲገመገም ግምገማው ተካሄደ፡፡ የግምገማውን ውጤት ለመድረክ ሰጠን፡፡ በወቅቱ ቴክኒካዊ የሆነ አንድ ችግር ተፈጠረ፡፡ በወቅቱ የግምገማው ውጤት መድረክ ዘንድ ሳይደርስ ሾልኮ ጋዜጣ ላይ ወጣ፡፡ ቅሬታው የተፈጠረው እዚያ ላይ ነው፡፡ የሚያጣላን የጥናቱ ፍሬ ነገር አይደለም፡፡ የግምገማው ዓላማ መድረክ ካለበት የቆመ የፖለቲካ ሁኔታ ተነስቶ መንቀሳቀስ ካለበት ምን እናድርግ የሚለውን ለማመላከት ነው፡፡

መድረክ ሲባል አንድነትንም ይጨምራል፡፡ የፖለቲካ ሥራ መሥራት ባለመቻላችን ሕዝቡን ልናንቀሳቅስ አልቻልንም እንፈትሸው ተባለ፡፡ መድረክ ካለበት እንዲያኮበኩብ ለማድረግ ነው፡፡ እኔም የአጥኝው ቡድን አባል ስለነበርኩ አውቀዋለሁ፡፡ ግን መጀመሪያ በጋዜጣ ከመውጣቱ በፊት ለመድረክ መድረስ ነበረበት፤ ቀጥሎም መምከር ነበረብን በሚል ነው፡፡

ይኼ ማለት ግን አካሄዱ ችግር ነበረበት ማለት እንጂ የግምገማው ፍሬ ነገር ልክ አይደለም ማለት አይደለም፡፡ በዚህ ነው እንግዲህ መሻከር የመጣው፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን እያረገብነው ነው፡፡ ነገር ግን በተወሰኑ ሰዎች ብቻ ችግሮች አይረግቡም፡፡ ያልሆነ ሚና ወስደው የሚጫወቱም አሉ፡፡ ያ አንዳንዴ ችግሩን ያሰፋዋል፡፡ በዚህ በኩልም ጋዜጦችም ጉዳዩ እንዳይበርድ ትፈልጋላችሁ፡፡ ኢሕአዴግም ይፈልጋል፡፡  
  
ሪፖርተር፡- ስለዚህ ችግራችሁን ስላልፈታችሁ ነው እናንተ ከመድረክ ተለይታችሁ የፖለቲካ ቅስቀሳ የጀመራችሁት?

አቶ አስራት፡- ፕሮግራምና ደንብ አለን፡፡ በደንባችን መሠረት የፓርቲው ነፃነት አለ፡፡ ውህደት አልፈጸምንም፡፡ መድረክ ግንባር ነው፡፡ እንደ ግንባርነቱም መድረክ በጋራ ካቀደው ሰላማዊ ሠልፍም ሆነ ስብሰባ ውጭ ፓርቲዎች ሊያካሂዱ ይችላሉ፡፡ በጋራ ያቀድናቸውን በጋራ እናካሂዳለን፡፡ መድረክ አቅሙ ውስን ነው፡፡ አንድነት ደግሞ በራሱ የተሻለ የፋይናንስ አቅም አለው፡፡ ከአባላት መዋጮና ከውጭም ድጋፍ አለው፡፡ [መድረክ] በዚያው ፍጥነት መሄድ አልቻለም፤ አልፈለገምም፡፡ 
 
ሪፖርተር፡- የፖለቲካ ቅስቀሳችሁን የጀመራችሁት በክልል ከተሞች ነው፡፡ ብዙ ጊዜ አዲስ አበባ ላይ ነበር የዚህ ዓይነቱን ሥራ ስትሠሩ የምትስተዋሉት፡፡ የስትራቴጂ ለውጥ አለ? ማግኘት የፈለጋችሁት ውጤትስ ምንድነው?

አቶ አስራት፡- ግብረ ኃይሉ የተሻለ ይመልሰው ነበር፡፡ ግብረ ኃይሉ ይህን ሲያቅድ ፈትሾ ገምግሞ ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡ ነገር ግን ጎንደርና ደሴ በተደጋጋሚ ጥያቄ በማቅረባቸው ነው፡፡ ከተሞቹ በተደጋጋሚ ጠይቀዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ነው ብዬ አስባለሁ፡፡

አዲስ አበባ ላይ ለማካሄድ እየሞከርን ነው፡፡ ካነሳህልኝ ያለንበትን ችግር ልግለጽልህ፡፡ ባለፈው በራሪ ወረቀቶችንና ማስታወቂያዎችን ለማሠራጨት ከፍተኛ እንቅስቃሴ አድርገናል፡፡ እንቅስቃሴ ውስጥ ስንገባ ቀጥታ ወደ ሰላማዊ ሠልፉ ለመግባት ነበር፡፡ ነገር ግን በጭራሽ ሊያላውሱን አልቻሉም፡፡ በሁለት ቀናት ውስጥ 42 አባሎቻችን ተያዙብን፡፡ ሲያዙ በራሪ ወረቀት በተናችሁ ነው የተባሉት፡፡ በራሪ ወረቀቱ ለሚቀጥለው ሰላማዊ ሠልፍ ሕዝባዊ ስብሰባ ለመጥራት መንደርደሪያ መንገዳችን ነው፡፡

 ፈርሜ የላኩትን አዳራሽ ለማግኘት የሚጠይቁ ደብዳቤዎችን ብዛት ብታይ ታዝናለህ፡፡ ከ30 በላይ ናቸው፡፡ የተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2000 አንቀጽ 46 ለፓርቲዎች የዕለት ተዕለት ተግባር ማከናወኛ የሚሰጥ ድጋፍ ስለሚመራበት አሠራር ይደነግጋል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ የሚሰጠውን ድጋፍ ለተመደበለት ተግባር ብቻ ማዋል አለበት ይላል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ የዕለት ተዕለት ተግባር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡ አንዱ የሕዝቡን የፖለቲካ ግንዛቤ ማዳበር፤ የፓርቲውን ዓላማ ለሕዝብ ማስረፅ፡፡ ዜጎች በአገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው መቀስቀስን ያካትታል፡፡

ይህ በራሪ ወረቀት የሚሠራው ይኼንን ነው፡፡ 42 አባላቶቻችን የተያዙት ፈቃድ የላችሁም ተብሎ ነው፡፡ ስለዚህ የፖለቲካ ሥራ ማከናወን እንዳንችል የሚያደርገን አየር እየፈጠሩ ነው፡፡ ከሚመለከተው የመንግሥት አካል ጋር በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር ጥያቄ አቅርበን በተደጋጋሚ በራቸውን አንኳኳን እስካሁን ምላሽ የለም፡፡
    
ሪፖርተር
Posted: 28 Jul 2013 02:26 PM PDT

July 28, 2013

The Horn Times Newsletter July 28, 2013
by Getahune Bekele, South Africa

Massive crackdown underway on opposition stronghold of South Wollo, Ethiopia

It was a pre-dawn assault by hundreds of heavily armed federal police members backed by pro-TPLF local militia on the opposition UDJP strong hold of South Wollo province.Massive crackdown underway on opposition in Ethiopia
According to Finotenetsanet newspaper reporters, yesterday’s dawn- to- dusk raid targeted the twin towns of Haiq and Worebabu; and more heavy handed attacks are set to continue in other nearby towns and villages of the historic province.
Worebabu area UDJP leader Ato Edris Saed told Finotenetsanet that the police tried to disguise their act by telling people that they are looking for weapons.
Arage Hussein, UDJP’s financial officer in the town of Haiq said the police and the feared local militia searched the homes of all 16 members of UDJP leadership, each search lasting for up to two hours and more.
“I pleaded with the five police men and the militias who came to my home at dawn that I am a man of peace and never owned a firearm but they proceeded with the search and left empty-handed.” Ato Arage Added.
Moreover, according to South Wollo zone UDJP chairman Ato Bisrat Abi, the ruling party is on a campaign trail in the area, on a burgeoning run to discredit the UDJP leadership and its members. TPLF cadres have already organized anti UDJP meetings and demonstrations as part of the well planned crack down on dissenting voices in the region.
“Since the recent mass anti TPLF rallies organized in Dessie and Gonder cities, UDJP has been on the rise. The ruling junta’s cadres now have an implacable enemy right under their noses with the potential of bringing down the conjugal dictatorship. Therefore, I see it as normal for the authoritarian and corruption-ridden regime to wage an all-out war on the UDJP.” A respected political analyst who requested anonymity told the Horn Times from Addis Ababa.
Asked if UDJP has any chance of surviving the onslaught with no international support, with western powers still generously endowing the ruling minority junta; turning a blind eye on its undemocratic practices, the elderly analyst said it is up to the people of Ethiopia to rally around the party and its young and energetic leadership.
“Look, we all thought UDJP was hanging on life support system after the loss of its patriotic leaders in Andualem Arage and Natinael Mekonnen. Am astonished by how the current young leaders filled the leadership vacuum and make the party grow from strength to strength. I hope they will keep the momentum, keep the pressure on the junta and get serious violations and abuses such as this one in south Wollo quickly to the media. We are in better times today than yesterday.”
Posted: 28 Jul 2013 02:52 PM PDT

July 28, 2013

by Selam Beyene, PhD
Ethiopian infantrymen running during battle in. Oct 1935.


Ethiopian infantrymen during battle. Oct 1935. PHOTO AP

The history of Ethiopia is replete with contradictions and paradoxes. There are accounts galore of heroism and meekness, patriotism and treachery, devotion and apathy, and, above all, fear of God and acts of brutality in that ancient country. These chronicles may help provide clues about the root causes of the Woyane anti-Ethiopia schema and the appropriate plan of action needed to deracinate them.
By anti-Ethiopianism we purport the systematic and government-sanctioned weakening of the national fabric by pitting one ethnic group against another, as was witnessed recently in such areas as Benishangul-Gumuz and Gura Ferda zones. Anti-Ethiopianism is the appalling government policy of dislocating natives from their ancestral lands and transferring national wealth to foreigners at dirt cheap prices. It is anti-Ethiopianism to frame a constitution whose central object is to promote the disintegration and land-lockedness of the country.  Most importantly, anti-Ethiopianism implies the deviant system of government under which all major economic, political and military institutions are controlled by the minority Woyane group, and through which fundamental human rights are suppressed and the people are denied their basic rights to participate in free and fair elections.
Confucius sagaciously advised: “Study the past if you would define the future.” Accordingly, when we consider the current predicaments of the country, which are characterized by ethnocentrism, totalitarianism, corruption, nepotism and absence of a feeling of Ethiopian patriotism amongst the rulers; and, most importantly, when we search for a viable solution to them, we should go no further for clues and explanations than the recent past events, beginning with the invasion of Italy in 1935-1940.
Basha Asress Tessema Meles Zenawi's grandfatherMuch has been documented about the infamous Fascist aggression by notable Ethiopian and Western historians, journalists and novelists, as well as other writers who had taken active parts in the actual war. While well-researched history books and journal articles may serve as the ultimate sources for academic exercise, there is considerable information that may be gleaned from anecdotal accounts narrated by individuals based on their personal experiences. In this regard, we are fortunate to have at our disposal now the writings of three foreigners who had the opportunity to witness firsthand the savagery of the Fascist aggression, the heroism of the Ethiopian fighters, and the betrayal by local collaborators.


Photos of Basha Asress Tessema (Meles Zenawi’s grandfather) flanked by a soldier of Mussolini

The three foreigners, whose paths had crossed several times in the battles of Tembien, Maichew and other fronts, had fought on the side of Ethiopia under the leaderships of such eminent Ethiopians as Ras Kassa Hailu Darge, Ras Seyoum Mengesha and Ras Mulugeta Yiggezu, the War Minister.

 In so doing, they were able to record considerable historical data and to leave behind intriguing accounts of bravery and treachery that could inform present and future researchers seeking answers to some of the most complex questions about present-day Ethiopia. Most importantly, they provide critical insights into the underlying reasons for the anti-Ethiopian agenda Zenawi and his Woyane entourage successfully exploited to catapult themselves to power; the continued damage to the long-term viability of the country that is caused by the misguided fiscal, economic, educational and military policies implemented by the TPLF-led regime; and the institutionalization of ethnic-based governance that is portentously promoted to nurture inter-ethnic animosity among brothers and sisters who have lived in relative harmony for many centuries.
Recently, the works of two of the foreigners were made accessible to Amharic readers. The first, ቀይ አንበሳ (Alpha, 2003) was translated by Tesfaye M. Bayileyegn from the original narration of Colonel Alejandro del Valle1. The second book, የሃበሻ ጀብዱ (AAU Press, 2010), is a translation by Techane J. Mekonnen based on Adolf Parlesack’s memoir in Czech entitled Habesska Odyssea (Praha : Panorama, 1989). The third, and most controversial, memoir was written by Colonel Feodor Konovalov, a Russian military adviser to Ras Seyoum Mengesha and other leaders. While there is no accessible Amharic translation of Konovalov’s writings, relevant excerpts are available in various sources (see, e.g., Clarke III, 2008 2).
Excepting a few and infrequent inconsistencies among the renditions of the three foreigners about shared events that they had jointly witnessed, there is a remarkable degree of consistency in their accounts of the breathtaking gallantry of Ethiopian fighters, as well as the distressingly heartrending treachery of domestic collaborators, especially from Tigray, Rayya, and Azebo regions, in the early days of the war.

Although Konovalov was generally silent on the contribution of the traitors to the defeat of Ethiopia, he was in remarkable concord with the other two in expressing awe and admiration at the inimitable valor and fearlessness of the Ethiopian army in the face of an infinitely better armed enemy. Quoting a Western diplomat, Konovalov was unhesitant to affirm: “… the Ethiopian soldier, well-taught and well-led, had no equal anywhere in the world.” The memoirs of all three abound with their eyewitness accounts of how, defying all odds against them, waves of primitively armed Ethiopian fighters, composed of men and women from every ethnic group, religious persuasion and social ladder, stormed, time and again, well fortified Italian positions, sending terror and confusion among the enemy. As one reads about the surreal exploits of those brave fighters, the knowledge of belonging to a people of such valiance and heroism fills one’s heart with a sense of immense pride. 

In one instance, for example, del Valle tells of a story in which the Ethiopians ferociously and unstoppably climbed up a hill to engage the enemy that was assailing them from above with automatic weapons and mustard gas. In summarizing his amazement at the extraordinary scene he was witnessing, he wrote: “The efforts of the invaders to try to stop those brave Ethiopians, who were charging uphill over the bodies of their fallen compatriots, was like firing bullets from machine guns to futilely slow down the gushing of water downhill.”
The foreigners also documented heroic accomplishments of ordinary citizens, whose names never made it to the history books, but who had demonstrated unimaginable bravery on the battlefields. Among such stories eloquently told by Parlesack, none is probably as fascinating as that of a young Oromo boy from the Sellale region by the name of Abichou. Parlesack describes with a Homeric touch the valiance of the boy as he terrorized the Fascist aggressors, chased to their deaths many of the traitors, coordinated a multi-ethnic army from Hamassen, Tigray, Gojjam and Sellale, and scored countless victories against the invading army.
Parlesack and del Valle were also unreserved in their expression of disgust at the degree of betrayal and treachery perpetrated by some members of the Tigray, Rayya and Azebo regions that made the campaigns of the great armies of Ras Seyoum, Ras Kassa and Ras Mulugetta immeasurably arduous. Parlesack even hinted that the balance of power at the battle of Maichew was tipped in favor of the invaders, thanks in great part to the sabotage of the traitors from Rayya and Azebo, who inflicted considerable damage on the advancing Ethiopian army coming from behind at critical moments.
Among the most notorious traitors of the era was Dejazmach Haile Sellasie GugsaAmong the most notorious traitors of the era was Dejazmach Haile Sellasie Gugsa, a great grandson of Emperor Yohannis IV, who gave his allegiance to Benito Mussolini in the early days of the war. This traitor facilitated the invasion of Mekelle in November of 1935, and later joined the invading army that marched on Addis Ababa in April of 1936.


Among the most notorious traitors of the era was Dejazmach Haile Sellasie Gugsa, a great grandson of Emperor Yohannis IV

Throughout the occupation, he provided invaluable service as a trusted adviser to both Rodolfo Graziani and the Duke of Aosta. Remarkably, his first demonstration of treachery was to raise the Italian flag in Mekelle, desecrating the Ethiopian tri-colors. Over six decades later, another traitor, the late Meles Zenawi, would defile that same flag.

Indeed, in the face of the well-known anti-Ethiopian sentiment unabashedly exhibited by Zenawi, and now aggressively implemented by his successors, it is not beyond the realm of rational proclivity to wonder whether the turncoats of the Italo-Ethiopian war did not influence the imprudent minds of the current traitors.

Much has been disclosed about the dubious family tree of the late dictator and the backgrounds of some of those in the Woyane leadership. Regarding the notorious heritage of Zenawi, Gebremedhin Araya, a one-time TPLF fighter and an accomplished authority on the late dictator’s family history, has given gripping testimonials, in a series of ESAT interviews, how the dictator’s mind might have been poisoned while growing up in a family that had always betrayed the land they lived in. There are also troubling accounts of the backgrounds of most of the Woyane leaders, including the notorious Bereket Simon, Sibhat Negga and several others.
At a time when there is a lot of confusion among some sectors of the Ethiopian community about the true nature of the Woyane regime and its hidden agenda, it is absolutely critical to see the treachery of the rulers through the prism of their treasonous forefathers. This is especially indispensable in any effort to raise the awareness of the people of Tigray in whose name these traitors are causing immeasurable damage. Although there were several traitors who, like Haile Sellasie Gugsa, sided with the enemy and fought against the Ethiopian army, there were also exemplary patriots from the same region who valiantly fought and died in defense of their motherland against Fascist invasion. Similarly, despite the common perception that many Tigreans today are backers of the evil dictatorship, it should be incontrovertibly affirmed that there is a large proportion of Tigreans who abhor the destructive and anti-Ethiopian path followed by the Woyane regime.
The late dictator and his party have always projected themselves as saviors of the people from the tyrannical rule of the Derg. Unfortunately, many genuine Ethiopians have overlooked the fact that the Woyane regime is not only a most vicious authoritarian system, as the Derg was, but also an atrocious organization whose ultimate objective is the destruction of Ethiopia as a nation. In actual fact, no rational government in history has unilaterally advocated the dismemberment of the country it rules, made attempts to justify its isolation through land-lockedness, parceled out precious lands to foreigners at dirt cheap prices, or systematically used ethnicity, famine, illiteracy and disease as instruments to enslave the people it governs, to the extent the Woyane rulers have done so. It is therefore vitally important to effectively establish the anti-Ethiopian identity of the regime, and to reignite the patriotism of those members of the society who have been hoodwinked by the pervasive propaganda campaign that the regime has successfully, but spitefully, launched to portray itself as a better alternative to the brutal Derg dictatorship.

A major weakness of the pro-democracy movement thus far has been its hopeless ineptitude to articulate precisely why the Woyane philosophy is anti-Ethiopian, and how dangerous that philosophy is to the long-term viability of the country. The suppression of basic human rights, the codification of ethnocentrism in the constitution, the irresponsible policy of land grabs, the pitting of one ethnic group against another, and the unfettered corruption among the leaders of the regime have not been effectively communicated to the people as manifestations of this general scheme of anti-Ethiopianism that the Woyane leadership has perfected over the past several decades
Indubitably, the only realistic strategy that would guarantee the certain destruction of the Woyane regime is one that successfully establishes and communicates to the people of Ethiopia this abhorrent nature of the regime. Without a thorough understanding of the TPLF as a perfidious organization by the people of Ethiopia in general, and those of Tigray in particular, there cannot be a unified front that is a prerequisite for a successful outcome of the struggle to save the country, liberate the oppressed, and establish a democratic system where individual freedoms would flourish and the long-term survival of Ethiopia would be guaranteed. As they have heroically demonstrated to the world before, during and after the Italo-Ethiopian war, there is nothing that unifies and arouses the fighting spirit of the people of Ethiopia more than a sense of direct threat to their heritage and independence either by foreign aggressors or domestic connivers. Pro-democracy forces, Websites, and other groups and individuals, therefore, have the moral imperative to reignite the ardor of the people to defend their country by raising their awareness as to the true nature of the treasonous organization that is Woyane.

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar