torsdag 21. februar 2013

በአዲስ አበባ የፍተሻና የዝርፊያ አቤቱታ


ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ልዩ አካባቢዎች “በሙስሊሙ ማኅበረሰብ አባላት ላይ ያነጣጠረ የቤት ለቤት ፍተሻና ዘረፋ እየተካሄደ ነው” የሚል ጥቆማ በደረሰን መሠረት ሁኔታውን ለማጣራት ሞክረናል። በጥቆማው መሠረት በሌሊት ፍተሻ የተሠማሩት ሰዎች ማንነታቸውን እንደሚደብቁና የጥቃቱ ሰለባዎች ደግሞ፥ በየካና ቦሌ ክፍለ ከተሞች፥ በኮልፌ ቀራንዮ፥ ቤቴልና አካባቢው ሠፈሮች የሚኖሩ ሙስሊሞች ናቸው።
ሙስሊሞቹ ይህ በዘመቻ መልክ እየተፈፀመብን ነው ያሉት የቤት ፍተሻና ዝርፊያ በእርግጥ እየተካሄደ ነወይ? ከሆነስ ለምንና ባሁኑ ወቅት ይካሄዳል?
እነዚህንና ሌሎች ጥያቄዎች ይዘን ማምሻውን የጥቃቱ ሰለባ ሆነናል ወደሚሉ ሰዎችና ፖሊስ ደውለን ነበር።
ሰሎሞን ክፍሌ ነው ዘገባውን ያጠናቀረው፤ ያዳምጡት

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar