tirsdag 22. januar 2013
ሰበር ዜና: በኤርትራ መፈንቅለ መንግስት ተካሄደ
ኢ.ኤም.ኤፍ. – የኤርትራ መከላከያ ሰራዊተ በዛሬው እለት (ሰኞ 21 ጃንዋሪ) በፕ/ት ኢሳያስ አፈወርቂ ላይ መፈንቅለ-መንግስት ማድረጉን ኢ.ኤም. ኤፍ. ከአስመራ በስልክ አረጋግጧል:: ሰራዊቱ በአሁን ሰዓት ማስታወቂያ ሚኒስትሩን የተቆጣጠረ ሲሆን እስካሁን ምንም አይነት ደም መፋሰስ እንደሌለ ዘጋቢያችን ገልጿል::
ኢሳያስ አፈወርቂ የት እንዳሉ የታወቀ ነገር የለም::
ምንጮች እንደሚሉት ኢሳያስ አፈወርቂ ለስራ ጉብኝት ምጽዋ ሲሆኑ ከአስመራ-ምጽዋ የሚወስደው መንገድም በወታደሮች ዝግ ሆኗል::
ወታደሮቹ በተለይ የኤርትራ ጋዜጠኞች ምንም እንቅስቃሴ እንዳያድርጉ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል:: ጋዜጠኛዋ የኢሳያስ አፈወርቂ ልጅም እንደታገተች ተገልጿል::
እንደ ሪፖርተራችን ዘገባ ህዝቡ እንዲረጋጋነ እቤቱ እንዲቀመጥ ሰራዊቱ እየተናገረ ሲሆን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሙሉ ተቋርጠዋል::
ምንም ደም መፋሰስ ሳይኖር ማስታወቂያ ሚ/ርን እስከመቆጣጠር መድረስ ያልተለመደ መፈንቅለ-መንግስት ነው::
የአፍሪካ ጥናት አኤክስፐርት የሆነው ማርቲን ፕላውት ዲፕሎማቲክ ምንጮችን በመጥቀስ መፈንቅለ መንግስት እየተካሄደ መሆኑን በድረ-ገጹ ጽፏል:: ከፈረንሳዩ ኤ.ኤፍ.ፒ. በስተቀር አለም አቀፍ የዜና ምንጮች ዜናውን አልዘገቡትም::
ዝርዝር ዘገባውን እየተከታተልን እናቀርባለን::
http://ethioforum.org/
Abonner på:
Legg inn kommentarer (Atom)
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar