tirsdag 29. januar 2013

በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ 13 ሚሊዮን ብር በማውጣት ፎርጅድ ቀለሞችን የገዙ ሰዎች ተያዙ


ጥር ፳ (ሀያ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ከዩኒቨርስቲው ምንጮች ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው በዩኒቨርስቲው ፋይናንስና ሂውማን ሪሶርስ ክፍል ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች 13 ሚሊዮን ብር ዋጋ የሚያወጣ ፎርጅድ ( የተጭበረበረ)የፕሪንተር ቀለምና የኮምፒተር እቃዎችን ገዝተዋል ተብለው በፌደራል ፖሊሶች ቁጥጥር ስር ውለዋል። የተያዙት ግለሰቦች ከዚህ ቀደም በከፍተኛ የሀላፊነት ቦታዎች ላይ የነበሩና ላለፉት 20 አመታት በተለያዩ መንገዶች ለአካባቢው ህዝብ የሚላከውን ገንዘብ በመዝረፍ የሚታወቁ ናቸው።
አንድ ስማቸው እንዳይገለጥ የፈለጉ ሰው እንደተናገሩት ገቢው በቀን አንድ ዶላር በሆነባት አገር ፣ ይህን ያክል የገንዘብ ዝርፊያ መካሄዱ አስገራሚ ነው ብለዋል። ግለሰቦቹ የኢህአዴግ ባለስልጣናት በመሆናቸው ህዝቡን ለማስደሰት ተብለው ታሰሩ እንጅ በቅርቡ ሊለቀቁ ይችላሉ በማለት ግለሰቡ አክለው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው ሙስና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄድ ላይ ነው።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar