torsdag 17. april 2014

አቶ ኦባንግ ሜቶ እና አቶ አብዱላሂ ሁሴን በኖርዌይ ኦስሎ ከኢትዮጵያውያንና ከኖርዌጅያን ባለስልጣናት ጋር ተወያዩ

Posted: 09 Mar 2014 12:28 PM PDT

አቶ ኦባንግ ሜቶ የአዲሲትዋ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ፓሬዝዳንትና አቶ አብዱላሂ ሁሴን የኦጋዴን ክልል ፕሬዝዳንት አማካሪ የነበሩና በክልሉየሚደረገውን የህዝብ ጭቆና፥ እንግልት፥ ግድያ የሚያሳዪ ወደ መቶ ሰአታት የሚደርሱ የቪዲዮ ማስረጃዎችን ይዘው በመሰደድ ለአለም ህዝብእያጋለጡ ያሉና በአሁኑ ሰአት በስዊድን ሃገር የፖለቲካ ጥገኝነት አጊንተው የሚኖሩ ሲሆን ከማርች 6 እስከ ማርች 7 ,2014 በነበራቸው የኖርዌይቆይታቸው ከተለያዩ የኖርዌይ ባለስልጣናት ጋር በሃገራችን ውስጥ ስለሚደረገው የሰብአዊ መብት ረገጣ በማስረጃ በተደገፈ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፥በመቀጠልም በነበራቸው ቆይታ ስፖንሰር አድርገው ባመጧቸው Solveig Syversen በተባሉ አክቲቪስትና እንዲሁም  Frontline Club Osloበተሰኘ ድርጅት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኖርዌጂያንና ኢትዮጵያውያን Filmenshus በተባለ ቦታ ተገኝተውበኢትዮጵያ ውስጥ እየተደረገ ያለውን የሰብአዊ መብት ረገጣ በማስረጃ በተደገፈ ለህዝብ ያቀረቡ ሲሆን ከታዳሚውም በተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች ላይውይይት ያደረጉ ሲሆን፥
                                      
 
                        
ማርች 7/2014 የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አጋጣሚውን በመጠቀም በጠራው አስቸኴይ ስብሰባ አቶ ኦባን ሜቶ እናአቶ አብዱላሂ ሁሴን ከኢትዮጵያውያኑ ጋር ሰፋ ያለ ውይይት ያረጉ ሲሆን በቀጣይም በሃገራችን እየተደረገ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት፥ ግድያ፥እስራት ለማስቆም ምን መሰራት አለበት በሚሉት አንገብጋቢ ነጥቦች ዙሪያ ከታዳሚውም ከእንግዶቹም የተለያዩ ሃሳቦች ላይ ሰፊ ውይይት ከተደረገበኋላ አቶ አብዱላሂ ሲያጠቃልሉ ያለብንን ችግር ለመፍታት የርስ በርስ ሽኩቻችንን ትተን ትኩረታችንን ሃገራችንን እያመሰ ያለው የወያኔ መንግስትላይ እናርግ በማለት ምክራቸውን የለገሱ ሲሆን አቶ ኦባን በበኩላቸው እነዚህ በአቶ አብዱላሂ ሁሴን ከሃገር የወጡት ማስረጃዎች በጣም ተቃሚማስረጃዎቻችን እንደሆኑና ወደፊት ጊዜው ሲደርስ መጠየቅ ያለባቸው አካላት ሃላፊነት እንደሚወስዱበት ጠቁመው ነፃነታችንን ለማስመለስሁላችንም መታገል እንዳለብንና የውጩ አለም እኛን ነፃ ያወጣናል ብለን ዝም ብለን መቀመጥ እንደሌለብን ያሳሰቡ ሲሆን፥በመጨረሻም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ዋና /አቶ ዮሃንስ አለሙ ለታዳሚዎችንና ለእንግዶቹ  ምስጋናበማቅረብ በአጭር ግዜ በተጠራ የውይይት መድረክ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን መገኘታቸውን አድንቀው ለቀጣይ በጋራ ሊሰሩ ስለሚችሉ ስራዎችግኑኝነት እንደሚቀጥልና ድርጅታቸውም በማንኛውም ስራ ላይ በግንባር ቀደምነት በሩን ከፍቶ እንደሚጠብቅ ገልፀው ስብሰባው ተጠናቋል፥፥

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar