lørdag 13. april 2013

ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ዛሬም በጽናት ትግላቸውን ቀጥለዋል በትናንትናው እለትም ፍትህ ይሰጠን በማለት ተቃውሞ ሲያሰሙ ዋሉ



ላለፉት አስራ አራት ወራት በጽናት ድምጻችን ይሰማ የሚል መፈክር አንግበው ዘረኛውን የወያኔ አገዛዝ አስጨንቀው የሚገኙ ሙስሊሞች በትናንትናው እለትም ተቃውሞአቸውን በመቀጠል የፍትህ ይሰጠን ጥያቄአቸውን ሲያሰሙ መዋላቸውን ዘጋቢያችን በላከልን ሪፖርት ገለጠ። እንደ ዘጋቢያችን ሪፖርት ሙስሊም ኢትዮጵያዊያኑ ቀደም ብሎ ሲያሰሙ ከነበረው የድምጻችን ይሰማ ጥያቄ ለወጥ ባለ መልኩ ፍትህ የሚል መሪ ቃልን ሲያሰሙ መዋላቸው ታውቋል።
በትናንትናው እለት በአዲስ አበባ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች “ፍትህ” የሚል ጽሁፍ የያዙ ወረቀቶችን በመያዝ ፍትህን በማለት ሲጠይቁ መዋላቸውን የገለጠው ዘጋቢያችን ፣ ፍትህ አጥተው በእስር ቤት የሚሰቃዩ መሪዎቻቸውን እጃቸውን በማጣመር በድጋሜ ሲያስቡ መዋላቸውን ገልጧል። እንደተለመደው በዚሁ የተቃውሞ ድምጽ አካባቢ በርካታ የፌደራል ፖሊስ አባላት ቢታዩም፣ ምንም አይነት ግጭት አለመፈጠሩን የደረሰን ሪፖርት አመልክቷል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ኢሳት በዘገባው እንዳመለከተው በአዳማ ፍትህ የጠየቁ ሙስሊሞች በፖሊሶች ተደብድበው እንዲባረሩ የተደረጉ ሲሆን በእስር ላይ በሚገኙት ሙስሊም መሪዎች ላይ ምንም አይነት ጠንካራ የሰነድም ሆነ የሰዎች ማስረጃ አለመቅረባቸውን ገልጧል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar