fredag 18. januar 2013

በስወች ላይ የሚደረገው የስባዊ መብት ረግጣ ይቁም


     
በሰሜን አሜሪካና በአውሮጳ የሚኖሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ የዓረና-መድረክ ደጋፊዎች በሀገራችን ያለው አደገኛ አዝማሚያና
ወቅታዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በፈረንጆች አቆጣጠር ጃንዋሪ 13/2013ዓ.ም ለ4  ሰዓታት ያህል የፈጀ የተሌ ኮንፈረስ ስብሰባ
አድርጓል። በተካሄደው ስብሰባ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በዜጎቻችን ላይ እያደረሰ ያለው የሰብኣዊ መብት
ጥሰት፣ እንግልት፣ ወከባና እስር በመሳሰሉት አንገብጋቢ ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ በሰፊው ተወያይቷል። በውይይቱ መደምደምያም
ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት፣ ለገዢው ፓርቲ መሪዎችና ደጋፊዎቻቸው፣ ለፍትሕና ለሰብኣዊ መብት የቆሙ ዓለም አቀፍ
ተቋማትና ታጋይ ሀይሎች፣ ለሀይማኖትና ሲቪክ ማሕበራት፣ እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚከተለውን የጋራ
መግለጫና ውሳኔ አስተላልፈዋል።
 ኢትዮጵያ በህወሓት/ኢሕአዴግ በአንድ ፈላጭ ቆራጭ ቡድናዊ አገዛዝ ስር ከወደቀችበት ቀን ጀምሮ እኖሆ ሁለት አሰርተ
ዓመታት አስቆጥራለች። ኢሕአዴግ ስልጣን ላይ ሲወጣ ካለፈው የተሻለ የዲሞክራሲ ለውጥ ይመጣል የሚል በብዙ ሰዎች ዘንድ
የተስፋ ጭላንጭል ተጥሎለት ቢኖርም “ጅብ እስኪነክስ ያነክስ” እንዲሉ ስልጣናቸውን ካደላደሉ በኋላ ግን ተስፋ የተጣለለትን
ዲሞክራሲ ደብዛውን በማጥፋት “ከፋፍለህ፣ በሆዱ ይዘህ፣ አሸብረህ፣ አደናግረህ፣ አናቁረህና አደንዝዘህ ግዛ” የሚለውን ሌሎች
ዲክታተራዊያን መንግስታት የሚከተሉትን የጡንቻ አገዛዝ ዘይቤ የዲሞክራሲ ሽፋን በመስጠት ዘላለማዊ ስልጣናቸውን
ለማጠናክር ሲሉ በበለጠ ሲጠቀሙበት መቆየታቸው የአደባባይ ሚስጢር ሆኖ ቆይቷል።
ዛሬ ከቀደሞ ጠቅላይ ሚኒስተር አቶ መለስ ዜናዊ ህልፈት በኋላም እሳቸው የተከሉትን ጨቋኝ ስርዓትና የአፈና መዋቀር እንዳለ
በመከተል በእግዚሄር ፍቃድ ያረፉትን መሪ የሳቸው ሞት ሌሎች ተቋዋሚ ድርጅቶች ዋጋ  እየከፈሉበት ይገኛሉ። በተለይም
ላለፉት 40 ዓመታት በህወሓት ሞኖፓላዊ አገዛዝ ስር ወድቆ በሆስቴጅ (ጅሆ) ተይዞ በሻዕቢያና በህወሓት መካከል አጣብቕኝ
ውስጥ ገብቶ በሁለት አለንጋ እየተገረፈ የሚገኘው የትግራይ ህዝብ ከወትሮው በባሰ መልኩ የአቶ መለስ ዕረፍት ዕዳ ከፋይና ሰለባ
ተቀባይ ሆኖ ይገኛል። ሰሞኑን በተለያየ ሚዲያ ሲገለፅ እንደሰነበተ ሁሉ ከራያ እስከ ሁመራ ድረስ በተለይም “በዓረና መደረክ”
አባላት ላይ በማነጣጠር በማሰር፣ በማስፈራራት፣ ፅሕፈት ቤታቸውን በመዝጋትና በመዝረፍ፣ ልሳናቸውን በመንጠቅና የተለያየ
መሰናክል በመፍጠር ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ ከፍተኛ ዘመቻ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።
የህወሓት መሪዎች የራሳቸው የግል የጓሮ ንብረት አድርገው የሚቆጣጠሩትን የትግራይ ህዝብ “ቢቸግረውም ከኛ አልፎ አቤት
የሚልበት ሌላ አማራጭ መንገድ የለውም፣ ወደደም ጠላም ከኛ ቁጥጥር አያልፍም” በሚል ንቀትና ትዕቢት የተነሳ ፓለቲካዊ
መብቱ ብቻ ሳይሆን የግል ስብእናውን፣ ማህበራዊ ፋብሪኩንና ቤት ንብረቱንም ጭምር  በግፍ እያፈራረሱት ይገኛሉ። ሰሞኑን
እንደተገለፀው በራያ አላማጣ ከተማ፣ በሁመራና በሌሎች የትግራይ ከተሞች የሚገኙ ወገኖቻችን ቤታቸው እየተናደና እየተፈናቀሉ
ይገኛሉ።
በዜጎች ላይ የሚፈፀመው የሰብኣዊ መብት ጥሰትና መፈናቀል በትግራይ ህዝብ ብቻ የተወሰነ አይደለም። በሌሎች ክፍላተ
ሀገርም ተመሳሳይ ግፍ እየተፈፀመ ይገኛል። የህወሓት/ኢሕአዴግ መንግስት በትግራይ  ላይ የጀመረውን ዘመቻ በማሀል ሀገርም
በመቀጠል በሌሎች የመድረክ አባላትና ጋዜጠኞች ላይ በሽብርተኝነት ስም ማሰር መደብደብና ማንገላታት አሁንም በሰፊው ስራየ
ብለው ተያይዘውታል። ከዚህም አልፈው በሀይማኖት ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ጣልቃ በመግባት በምእመናን ወገኖቻችን
ላይ እየተካሄደ ያለው የከፋፍለህና አናቁረህ ግዛ እርምጃ እየተባባሰ መምጣቱ ለብዙ ዜጎች አሳሳቢ ጉዳይ ሆኖ ይገኛል።    
                         የተከበራችሁ                                                  የተከበራችሁ  ውድ  ውድ  ውድውድ ኢትዮጵያውያን  ኢትዮጵያውያን  ሆይ  ሆይ!! ሆይሆይ!!  !!!!
 
የህወሓት/ኢሕአዴግ መሪዎች በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያላቸው የንቀትና የማንአለብኝነት ድርጊት በሰብኣዊ መብት ጥሰት ብቻ
የተወሰነ አይደለም። በሉዓላዊነታችን ላይ እየተዶለተ ያለው ሴራም በሀገራችን ላይ ያንጃበበ አደጋ መሆኑን ልብ ልነው ይገባል።
በተለይም በአቶ መለስ ዜናዊ ዘመን ድብቅ አጀንዳ ሆኖ በሚስጢር ይሰራበት የነበረ ጉዳይ አሁን በነ በረከት ስምዖን ጋሃድ እየሆነ
መጥቷል። አቶ በረከት ስምዖን በቅርቡ በኤርትራውያን መድረክ ላይ ተገኝቶ የዳር ድንበርንና ባድመን በሚመለከት ተጠይቆ
“ባድመ በሕግ ለኤርትራ የተሰጠ ስለሆነ ውሳኔው ቀደም ሲልም ተቀብለናል። ለወደፊትም የኛ ያልሆነውን መሬት የኛ ነው ብለን
መከራከር አንችልም። በሕግ አኳያም ተገቢ አይደለም። ስለዚህ ባድመ የኤርትራ መሬት መሆኑን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ
በማለት ሲገልፅ ስለ ባህር በር በሚመለከት ደግሞ የወደብ ጥያቄ የድሮ ህልመኞች (ኦልድ ስኩል) የሚያነሱት አጀንዳ እንጂ በዚሁ
ሰላሳ ዓመት ውስጥ ተወልዶ ያደገ ወጣት ኢትዮጵያዊ ጥያቄውም ጉዳዩም አይደለም ረስቶታል” ብለዋል። አቶ በረከት ንግግሩን
በመቀጠል “ቀድምም ቢሆን ከኤርትራ ጋር ወደ አላስፈላጊ ግጭትና ደም መፋሰስ እንድንገባ የገፋፉንና ኤርትራውያንን ከኢትዮጵያ
እንዲባረሩ ያነሳሱት ትምክህትና ጦረኛ አመለካከት ያላቸው እነ አቶ ገብሩ አስራትና እነ አቶ ስየ አብርሃ ናቸው እንጂ የኛ አካሄድና

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar