በኢትዮጵያ አንድም የፖለቲካ እስረኛ አለመኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በድፍረት ተናገሩ
የምዕራብ አገሮች በስፋት ኢንቨስትመንት ላይ ያልተሰማሩት በመንግሥት ችግር ሳይሆን በራሳቸው የኢኮኖሚ ቀውስ መሆኑንን በማመልክት አስተያየት ሰጡት አቶ ሃይለማርያም፣ ቻይናና ህንድ በኢትዮጵያ ከፍተኛውን የኢንቨስትመንት ዘርፍ እንደተቆጣጠሩት፣ በአነስተኛ ደረጃም ቢሆን የቱርክ ባለሃብቶች እየገቡ መሆኑን ገልጸዋል። ቻይናና ህንድ እያስመዘገቡ ያለው እድገት ከፍተኛ በመሆኑ በአሁኑ ሰዓት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በስፋት ኢንቨስትመንት ላይ መሳተፋቸውን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት 11.4 በመቶ መሆኑንን የዓለም ባንክ ማመኑንና የተጀመሩት ከፍተኛ የልማት ስራዎች በተያዘላቸው የአምስቱ ዓመት እቅድ መሰረት በርብርብ እንደሚሰራ አስታውቀዋል። በቤቶች ግንባታ “በአፍሪካ በዓመት 100ሺህ ቤቶች የሰራው ኢህአዴግና ኢህአዴግ የሚመራው መንግስት በቻ በመሆኑ ልንደነቅ ይገባል” ሲሉ በቤቶች ግንባታና ግንባታውን ለመቆጣጠር የተጀመረው አካሄድ በተጀመረው መልኩ ይቀጥላል ብለዋል። መንግሥታቸው ይህንን “ግንባታ” ሲያደርግ በየጊዜው ስለሚያፈርሰው የዜጎች ንብረትና ህይወት ከእርሳቸው የ“ልማትና ግንባታ” ንግግር ጋር የሚሄድ ባለመሆኑ ሳይጠቅሱት አልፈውታል፡፡
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar