ዶይቸ ቬለ
ጋዜጠኛ ጳዉሎስ ኞኞ በህይወት ዘመኑ ለአንባብያን ያበረከታቸዉ ሥራዎች ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ተበረከተ። የታዋቂዉን ጋዜጠኛና ደራሲ ሥራዎች ለተቋሙ ያበረከተዉ ልጁ ሐዋርያዉ ጳዉሎስ በግሉ ቤተመጻህፍት ለማቋቋም አቅሙ ባይፈቅድለት ኅብረተሰቡ ከዩኒቨርሲቲዉ እንዲያገኘዉና እንዲጠቀምበት አስቦ ለመስጠት መወሰኑን ገልጸል። በስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙ ታዳሚ ምሁራን የጳዉሎስ ኞኞን ስራዎች ሲዘረዝሩ በተለይ በጋዜጣ ላይ አንድ ጥያቄ አለኝ በሚለዉ አምዱ በወቅቱ የአዲስ ዘመን ጋዜጣን ቅጂ ቁጥር እንዲጨምር ማድረጉን አስታዉሰዋል።
|
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar