torsdag 17. januar 2013


የሀገር ጩኸት እና የታሳሪ ልጆች… አውደ-ዓመት
አጀንዳ- ፩
ለምን ይጮኸል?
መልሱ፣ ለምን አይጮኸም ይሆን? …በጠመንጃ አስገዳጅነት፣ ለማይጨበጥ፣ ለማይታይ ‹‹ራዕይ›› ሀገርን፣
ዘመንን፣ ትውልድን፣ እምነትን… ‹‹ገብር›› ሲባል ማን ነው የማይጮኸው? ... የመንግስት ሰራተኛው
ይጮኸል፣ የግል ተቀጣሪው ይጮኸል፣ ቀጣሪው ይጮኸል፣ ስራ እጡ ይጮኸል፣ ነጋዴው ይጮኸል፣ ሸማቹ
ይጮኸል፣ ሰራዊቱ ይጮኸል፣ ሙስሊሙ ይጮኸል፣ ክርስቲያኑ ይጮኸል፣ ጠንቋዩ ይጮኸል፣ እምነት
የሌለው ይጮኸል፣ የተደራጀው ይጮኸል፣ ያልተደራጀው ይጮኸል፣ የጠገበው ይጮኸል፣ የራበው
ይጮኸል፣ ፍትህ ያጣው ይጮኸል፣ እስረኛው ይጮኸል፣ እስረኛ ጠባቂው ይጮኸል፣ ታሪክ
ይጮኸል….ሰሚ አልባ ጩኸት! እሪ በከንቱ!!
ለዚህ ሁሉ ጩኸት ኃላፊነት መውሰድ አለበት የሚባለው መንግስት ‹‹መናገር እንጂ መስማት ተስኖታል›› በሚል ድምዳሜ መዝገቡ
ከተዘጋ ፀሀይ ጠልቃለች፡፡ በእርግጥ ያለፉት ስርዓታት መስማት የተሳናቸው ስለነበሩ ታሪክ ሆነው የመቅረት ዕጣ ገጥሟቸዋል፡፡ አፄ
ኃይለሥላሴ ‹‹ህዝባችን…›› እያሉ ያንቆለጳጵሱት የነበረውን ህዝብ አንድም ቀን አድምጠውት አያውቁም ነበር፡፡ ኮሎኔል መንግስቱም
የስልጣናቸው ምንጭ ‹‹ሰፊው ህዝብ እና ታሪክ የጣለባቸው አደራ›› እንደሆነ በየአደባባዩ ቢደሰኩሩም ከአፄው ያለመስማት ታሪክ
አልተማሩምና ከውድቀት ሊያመልጡ አልቻሉም፡፡ አቶ መለስ ዜናዊም ቤተ-መንግስት የገቡት ለ17 ዓመት በዱር በገደሉ በመታገላቸው
ሳይሆን፣ ብሔር ብሔረሰቦች ስለመረጧቸው መሆኑን ደግመው ደጋግመው መግለፃቸው የሚታወቅ ቢሆንም‹‹መረጡኝ›› ያሏቸውን
‹‹ብሄር ብሄረሰቦች›› ሲያደምጡ ታይተው አያውቁም፡፡ ተተኪዎቻቸውም ቢሆኑ የተለየ ድምፅ፣ የተለየ ሃሳብ ለማድመጥ አልተዘጋጁም፡፡
… ለዚህም ነው ዛሬም እሪ በከንቱው የቀጠለው (ያውም ‹‹የሚሰማው እከሌ ነው›› ተብሎ ጣት ሊጠቆምበት የሚችል መሪ በሌለበት
ሀገር)
የሆነ ሆኖ እንደ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት ወድቆ መነሳትን ችሎ ለለውጥ የታገለ ህዝብ ያለ አይመስለኝም፤ ተረኛውን ጨቋኝ ገዥ
(ብሔርንና ሀይማኖትን ሳይለይ) ታግሏል፤ እየታገለም ነው፡፡ ከስንት አንዴ በለስ ቀንቶት ማሸነፉ የተሳካለት እንደሆነም፣ ድሉን ጥቂት
ጨካኞች ይቀለብሱትና ታግሎ ወደ ጣለው ስርዓት ይመለስ ዘንድ ያስገድዱታል፡፡ አፄ ኃይለሥላሴ ልጅ እያሱን ታግለዋል፡፡ ‹‹ከስራ
ይልቅ ጨዋታና ፈንጠዚያ ያበዛሉ››፣ ‹‹ብዙውን ጊዜ ‹ችሎት›ስለማይሰየሙ አቤት ባይን ያንገላታሉ››፣ ‹‹የኢትዮጵያን መሰረት ሊንዱት
ነው››… የሚሉ ቅሬታዎችን በማራገብ መኳንንቱን አስነስተውባቸው ከስልጣን ካባረሯቸው በኋላ፣ ለአራት አስርት ዓመታት ሀገሪቱን
ያስተዳደሩት ከልጅ እያሱም በከፋ የጭቆናን ቀንበር በማሻከም ነበር፡፡
ከተማሪ እና አስተማሪ ጋር ተባብሮ አፄውን ‹‹ጨቋኝ››በሚል ከዙፋን የገለበጠው ደርግስ ቢሆን ስልጣን በእጁ ሲገባ ምንድር ነው
ያደረገው? ሰቆቃን፣ ሽብርን፣ እልቂትን፣ ድህነትን… በጅምላ ማከፋፈል ነበር፡፡ ደርጉን ‹‹ፋሽስት፣ ጨፍጫፊ›› በሚል የታገለው
ኢህአዴግስ ከድል በኋላ መንበረ ስልጣኑን ሲያደላድል ወዴት ተመለሰ? ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ ‹‹የቀንድ አውጣ ኑሮ›› በሚል ርዕስ
ባሳተመው የግጥም መድብል ላይ የገለፀው አይነት ነው የሆነው፡-
‹‹…አቶ እርገጤ ሄደው፣ አቶ እርገጤ መጡ፣
ከቀንድ አውጣ ዛጎል ላይ የሚቀመጡ፣
ነገደ ቀንድ አውጣ እንቅልፍህን ለጥልጥ፣
እንቀሳቀስ ብለህ ሰው እንዳትገለብጥ፣
ዛጎልህ ምቹ ነው፣ ከላይ ብሎ ጎበጥ፣
  ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar